Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ወንድምን አስቦ እርሱ በሌለበት ዱዓ ማድረግ ያለው ትሩፋት

👉 ((ወንድምን አስቦ እርሱ በሌለበት ዱዓ ማድረግ ያለው ትሩፋት))
▪️ የአላህ መልእክተኛ ﷺ  እንዲህ ብለዋል፦
“አንድ ሙስሊም የአላህ ባሪያ ወንድሙ በሌለበት(አስታውሶ) በሩቅ ዱዓእ ያደረገለት እንደሆነ መላኢካው “ላንተም ተመሣሣዩን።”ይለዋል።"
📚ሙስሊም (በሐዲስ ቁጥር  2732) ዘግበውታል።
ሸይኽ ዑሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
🔘"ወንድምህ አደራ ሳይልህ አስታውሰህ በሌለበት ዱዓ ማድረግህ ልቦናህ ውስጥ እውነተኛ እምነት እንዳለ አመላካች ነው። 
ምክንያቱም የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ፦"ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ እስካልወደደ የማናችሁም እምነት(ኢማን) የተሟላ አይደለም።" ብለዋልና። 
ስለዚህም እሱን አስበህ ዱኣ አድርግልኝ ብሎ ሳያዝህ ለርሱ ዱዓ ማድረግህ እሱን መውደድህና ብሎም ለራስህ የምትወደውን ለወንድምህ መውደድህ ጠቋሚ ነው።"
📗📙( ሸርሑ ሪያዱ ሷሊሒን 4/20―21)

Post a Comment

0 Comments