Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ድሃ ማነው⁉

ድሃ ማነው⁉

የአላህ መልክተኛ(ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ከዕለታት አንድ ቀን ከባለደረቦቻቸው ቁጭ ብለው ሳለ፦
 
“ድሃ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ?”  በማለት ይጠይቃሉ። 

ሰሐቦችም ፦

“እኛ ጋር ድሀ ማለት ምንም ንብረትና ገንዘብ የሌለው ነው።” በማለት ይመልሳሉ። 

የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ግን፦

 “ከኡመቴ ደሀ ማለት የትንሳኤ ቀን በብዙ ሰላቶች፤ ዘካዎችና፤ ፆሞች የሚመጣ ሰው ነው፣ግና ይህ ሰው 
※ አንድ ወንድሙን ሰድቧል፣ 
※ ሌላው ላይ ዋሽቷል፣
※ የአንዱን ገንዘብ ያለአግባብ ወስዷል፣
※ የሌላውን ደም አፍስሷል፣
※ አንዱን መትቷል፣ 
※ በሌላው ላይም ድንበር አልፏል፣ 

ያኔም (የትንሳኤ ምርመራ ቀን ) የራሱን ጥሩ ሥራዎች ለበደላቸው በካሳ መልክ አሳልፎ ይሰጣል፣ ጥሩ ሥራው ለመካሻ አልበቃ ይለውና የበደላቸውን ሰዎች ኃጢያት ይሸከማል። ከዚያም ወደ ጀሀነም ይወረወራል።”  በማለት መለሱላቸው። 

 (ሙስሊም ሐዲሥ ቁ.6531)

                ــــــ ❁ ❁❁ ❁ ــــــ      

Post a Comment

0 Comments