🏝 በዐርሽ ጥላ ሥር!
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
“በዚያ ከጥላው በስተቀር ምንም ጥላ በሌለበት ቀን (የፍርዱ ቀን) አላህ ሰባት ሰዎችን በዓርሽ ጥላ ስር ያኖራቸዋል።
እነርሱም፡-
1 ፍትሃዊ መሪን ፣
2 አላህን በመገዛት ወጣትነቱን ያሳለፈ፣
3 ልቡ ከመስጅድ ጋርየተቆራኘን ሰው፣
4 ለአላህ ብቻ ብለው በአላህ መንገድ ላይ የተዋደዱንና በርሱም መንገድ ላይ የተለያዩ ፣
5 አንዲት ቆንጆ ሴት ራሷን ለዝሙት አዘጋጅታለት ‘‘አላህን እፈራለሁ’’ በማለት እምቢ ያለ፣
6 በድብቅ ምጽዋት የሚሠጥ ሰው፣
7 ብቻውን ሆኖ አላህን ሲያስታውስ አላህን ፈርቶ ዓይኖቹ በእንባ የሚሞላና ጉንጮቹ የሚርሱ ሰው”
(ቡኻሪ ዘግበውታል።)
ــــــ ❁ ❁❁ ❁ ــــــ
0 Comments