Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ራያ አባ ሚጫ ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ኢኽዋኒ ዩሱፍ አልቀርዳዊ ጋር ምን ፈልጎ ነው አብሮት ፎቶ የሚነሳው?

Sadat Kemal Abu Meryem's photo.
ራያ አባ ሚጫ ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ኢኽዋኒ ዩሱፍ አልቀርዳዊ ጋር ምን ፈልጎ ነው አብሮት ፎቶ የሚነሳው?
ዩሱፍ አልቀርዳዊን ለማታውቁት የሚከተሉት ጥመቶችን የተሸከመ ሰው ነው፡፡
• የኩፍር ንግግሩ፡- የጁምዐ ሁለተኛ ኹጥባ ላይ የሚከተለውን ተናግሯል ‹‹ኹጥባዬን ጨርሼ ከመውረዴ በፊት ትንሽ ስለ እስራኤል ምርጫ መናገር እፈልጋለሁ፡፡ አረቡቹ በጠቅላላ ነዳህ ጲሪዝ ያሸንፋል ብለው ተስፋቸውን ጥለው ነበር፤ ነገር ግን ተሸነፈ፡፡ ከእስራኤል የምንወድላትም ይህንን ነው፡፡ የእኛም ሀገር እነደዚህች አገር እንድትሆን እንመኛለን እንፈልጋለን፡፡ በጥቂት ሰዎች አማካኝነት ሲመራ የነበረው ስልጣኑን አጥቷል፡፡ አገራችን ላይ እንደለመድነው 94% ወይንም 95% (ድምፅ) አይደለም ነገር ግን 99% (አዎን 99%፤ ምንድን ነው ይሄ?) አላህ ለሰው ልጆች እራሱን ተመራጭ አድርጎ ቢያቀርብ ይህንን ያህል ድምፅ አያገኝም ፡፡ይሄ (አረብ አገር ላይ የምናየው ምርጫ) ውሸት ማጭበርበር እና የመሳሰሉት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ እስራኤልን እሰየው እንላታለን››፡፡ ምድር በዚህ የኩፍር ንግግር አትሰነጠቅምን? ለሸይኽ ኢሰይሚን (አላህ ይዘንላቸውና) ይህ ቃል በድምፅ ተከፍቶላቸው ከሰሙ በኋላ የሚከተለውን ተናገሩ ‹‹በአላህ እጠበቃለሁ፡፡ ይህ ሰው መቶበት ግድ ይለዋል፤ እምቢ ካለ እንደ ሙርተድ (ሀይማኖቱን እንደከዳ ሰው) ይገደል፡፡ ፍጡራንን ከፋጣሪ ስላስበለጠ፡፡ ተውበት ካደረገ አላህ የባሪያውን ወንጀል መሀሪ ነው፤ ካልሆነ ውላቱል አምር (የሙስሊም መንግስት) አንገቱን (በሰይፍ) ይቀንጥሰው፡፡››
• ‹‹ከይሁዳዎችን ጋር የእምነት ጦርነት የለንም የመሬት እንጂ፡፡ ካሃዲያንን ካሃዲያን ስለሆኑ አይደለም የምንዋጋቸው መሪታችንና ቤቶቻችንን ያላግባብ ስለቀሙን እንጂ›› (አራያህ መፅሄት ቁጥር 4696፣ 24 ሸዕባን 1995 ኢ.አ)፡፡ አላህ እና መልክተኛው ምን እንደሚሉ እንስማ፡፡ ይሁዳዎች ከሰዎች ሁሉ ከነሳራም ለአማኞች ጠላትነታቸው የበረታ ነው አለህም እንዲህ ይላል ‹‹ለአማኞች ከጠላትነት በኩል ዩሁዳንና ጣዖታዊያንን ታገኛለህ››ሱረቱል ማኢዳ
• ዘፈንና ሙዚቃን መፍቀዱ፤ እንዲያውም ጥሩ ነገር ነው ማለቱን ‹‹አል ሀራም ወል ሀላል›› ‹‹ፈትዋ ሙዐሲራ›› እና በመሳሰሉ መፀሃፎቹ መግለፁ፡፡ እራሱ እንደተናገረው ‹‹የፋይዛ አህመድ፤ ሻዲያ፤ ኡሙ ኩልሱም፤ ፊሩዝ እና የመሳሰሉትን ሴቶች ዘፈን መከታተል ይወድ እንደነበር ጠቅሷለል›› (አራያህ የሚባል የኳታር መፅሄት ቁጥር 5969 ቀን 19/ ጁማዱል ኡላ 1419 ሂጅሪ)፡፡ ዘፈን ሃራም ለመሆኑ የነብያችን አንድ ሀዲስ ሀቅን ለሚፈልግ ትበቃዋከች ‹‹የአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁንና) ከኔ ኡመት ሰዎች ይመጣሉ ለወንድ ልጅ ሀር ልብስን የሚፈቅዱ፤ መጠጥን እና የሙዚቃ መሳሪያን የሚፈቅዱ›› ኢማሙ ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡ የአላህ ባሪያዎች እንደው እናንተው ፍረዱት፡፡
ኡለማዐል ኢስላም ከሰሃባዎች ጀምሮ፤ አቡ ሀኒፋ፤ ኢማሙ ማሊክ፤ ኢማሙ ሻፊዕ፤ ኢማሙ አህመድ፤ ሙሀዲስ ቡኻሪ፤ ሙስሊም ሁሉም በአንድነት ዘፈንን ከልክለዋል፡፡
ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ ‹‹እኛ ጋር ዘፈን የሚያዳምጥ ፋሲቅ ነው›› ታላቁ ሰሃባ አብደላህ ኢብን መስዑድ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እንዲህ ይላል ‹‹ዘፈን ማዳመጥ በቀልብ ኒፋቅን ያበቅላል ውሃ አዝርትን እንደሚያበቅል ሁሉ›› ፡፡ ቃዲ ኢያድ የተባሉ የማሊክ መዝሃብ ተከታይ ታላቅ አሊም ዘፈን ሀራም ለመሆኑ ኢጅማዕ ጠቅሰዋል፡፡
የሙዚቃ መሳሪያን አስመልክቶ ኢማሙ አህመድና አቡዳውድ የዘገቡት ሰሂህ ሀዲስ እንጨምር፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁን) ‹‹አላህ መጠጥን፤ ቁማርን፤ ከበሮ መምታትን ሀራም አደረገ›› ብለዋል፡፡
• የካቶሊኩ ፓፓስ በሞተ ጊዜ ‹‹አላህ ይማረው ማለቱ››፡፡ አላህ ግን መልክተኛውንም ሆነ አማኞችን ለነዛ በኩፍር ላይ ለሞቱ ሰዎች ምህረትን እንዳይጠይቁ አዟል፡፡
ዩሱፍ አልቀርዳዊ ይህንን እና ብዙ መሰል ከባባድ ስህተቶች አሉበት፡፡
የዩሱፍ አልቀርዳዊን አጥማሚነት ያላወቃችሁ ወንድም እና እህቶች ተጠንቀቁት፣ ወደ ተውሂድ ሳይሆን ወደ ፖለቲካ እና ወደ ጥመት የሚጣራ የፊትና ሰው ነው፡፡ አላህ ከጠሞ አጥማሚዎች ይጠብቀን፡፡