Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ቀብር ከፊት ለፊቱ ወይንም በዙሪያው ባለበት መስጂድ መስገድ ብይኑ ምንድነን ነው? መልሱን ከሰማሀቱ ሽይኽ አብዱል አዚዝ ኢብኑ ባዝ

Ibnu Muhammedzeyn's photo.
ቀብር ከፊት ለፊቱ ወይንም በዙሪያው ባለበት መስጂድ መስገድ ብይኑ ምንድነን ነው? መልሱን ከሰማሀቱ ሽይኽ አብዱል አዚዝ ኢብኑ ባዝ
=====================
ጥያቄ:- በመስጂድ ውስጥ: በዙሪያው: በቂብላው(ከፊት ለፊት) ቀብር ባለግዜ መሰገድ ብይኑ ምንድን ነው?
መልስ:- በመስጂድ ውስጥ ቀብር ካለ ቀብሩ ከሰጋጁ ሰው ፊት ለፊትም ይሁን ኋላ ወይም ከቀኙም ይሁን ከግራው ሶላቱ ተቀባይነት የለውም (ምክኒያቱም ለዚህ) ለነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም ንግግር ሲባል:- "አይሁዶችን እና ነሷራዎችን አሏህ ከራህመቱ ያርቃቸው የነብያቶቻቸውን ቀብር መስጂዶች አድርገው ያዙ:: ሀዲሱ በትክክለኝነቱ የተስማሙበት ነው::
"ንቁ ከናንተ በፊት የነበሩት የነብያቶቻቸውን እና የሷሊሆቻቸውን ቀብር መስጂዶች አድርገው የሚይዙ ነበሩ ንቁ ቀብሮችን መስጂዶች አድርጋችሁ እንዳትይዙ እኔ የዚህ (አይነቱን ስራ መስራትን) እከለክላችኋለሁ " ሙስሊም ሶሂህ ላይ አውርተውታል::
ከቀብር አጠገብ ሶላት መስገድ ከሽርክ መዳረሻዎች እና በቀብሩ ባልተቤት ድንበር ከማለፍ (ጭምርት) ስለሆነ
ለተጠቀሱትም ሁለት ሀዲሶች በነሱም ማእና(ትርጉም) ለመጣ ገዲስ (እነዲሁም) የሽርክን ቀዳዳ ለመዝጋት (ሲባል ከቀብር አጠገብ የሚሰግድን ሰው) መከልከል ግዴታ ሆነ::
ሽይኽ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁሏሁ ተአላ
ምንጭ:- ቱህፈቱል ኢኽዋን ሊብኒ ባዝ ገፅ 68 ጥያቄ ቁጥር 12