Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ማጭድና_ጥዱን_ቀንበርና_በሬውን_እናገና


‪#‎ማጭድና_ጥዱን_ቀንበርና_በሬውን_እናገናኝ‬
ይነበብ
ያዝ እንግዲህ…
አሕባሾች (በነሱ ቤት ‹‹ሃበሾች›› በኛ ቤት ‹‹ቁቡሪዮች››) ‘‘ማስተር-ማይንድድ’’ ንድፈ-ሃሳባዊ ሰው ለሆኑት ‘‘ሸኻቸው’’ ዐብዱላህ ሀረሪ (ውይ ‘‘ሸኻቸው’’ ነው እንዴ ያልኩት?) እሽ አለቃቸው (በፈረንጅኛ BOSSሳቸው) ወይ በቃ እሽ አረንጓዴ መብራታቸው ( ‘‘ልማታዊ ሙፍቲ’’ ሆነው እንዳይመስላቹ (ነገሩ ወዲህ ነው.. ። ቀብርን መማፀን ይቻላል? አረንጓዴ መብራት (ይቻላል መሆኑ ነው) ፣ በሞተ አካል መጠበቅ? አረንጓዴ መብራት ፣ ሴት ልጅ ሱሪ መልበስ ትችላለች ? አረንጓዴ መብራት ፣ ከፍናፍንት ጋር ግንኙነት? አረንጓዴ መብራት ፣ ለዚ ነው ። ተሳስተውም ቢጫም አያበሩ ሁሌ አረንጓዴ!))
እናማ! አሕባሾች ለአረንጓዴ መብራታቸው የሹመት መዐት ደርድረውላቸው.. (ምን ትዝ አላቹ ? የኛ ሃገሩ ጳጳሱ አላህ አይማረውና (አዎ አይማረውና! ‘‘ይማረው? አይማረው?’’ በኔ በኩል አይማረው! በነእንትና በኩል ለጳጳስ ‘‘ይማረው’’ ይባላል (እዚጋ ያዝልኝማ! ብኋላ አስታውስካለው) እሱ ትዝ አላቹ አይደል ? ። ትዝ ይላቿል ማታ ማታ 2፡00 ላይ ዜና አንባቢው ስሙን ሲጠራ? ‘‘ተረረረረረ…ረረ..’’ ‘‘ወዘተ..’’ ብሎ ቢያልፈው ምን ነበረበት?) ምን በሰው ሙድ እየያዝክ ትነፍራለህ የኛው ፋዘርም ጋር አለ’ኮ ።
ላሳይህ ?
ልጀምር ነው እሺ ተዘጋጅተካል ?
‹‹ አል ሙርሺደል ሙረቢ ፣ አል ወሊዩል ሷሊህ ፣ አል አሊሙል ጀሊል ፣ ቁድወቱል ሙሃቂቂን ፣ ዑምደቱል ሙደቂቂን ፣ ሰድሩል ኡለማዑል አለሚን ፣ አል ኢማሙል ሙሃዲስ (ቆይ አንዴ ልረፍ ኡ…ሕሕ… እሺ ልቀጥል) አል ተቂዩል ዟሂድ ፣ አል ፈድሉል ዐቢድ ፣ ሷሂቡል ሙዋሃቡል ጀሊል ፣ አል ሸይኽ አቡ ዐብዱረህማን (መጨረሻም ላይ) አል ሃረሪ (አንዳንዴም) ሃበሺ ›› ብሎ ያልቃል ።
ወታደር ቢሆኑ ምን ደረጃ ይደርሱ ነበር ? ‹‹አስር አለቃ ከዚያም አምሳ አለቃ ፣ ከዚያም መቶ ፣ ከዚያም ሺ (ምነው ሺ የለም እንዴ ?) ከዚያም ንጉስ ከዚያን ንጉሰ ነገስት ከዚያም ንጉሰ ነገስታት ወ-ነገስታት›› ብቻ ምን አለፋቹ ወዘተትረፈረፈፈ….. ።
ዛሬ ግን ማውራት የፈለግኩት ስለ ‘‘ሃያ ሹም’’ የሆኑትን ሃረሪ አይደለም ። ስለ ‘‘አስር ሹም’’ የሆኑት ቀረንዷዊን እንጂ ። ‘‘ቀረንዷንዊ ሰማንያ ምናምን አመት ሞላው!’’ ብለው እነ እገሌ በፌስቡክ ልደቱን እያከበሩለት ነው አሉ ። ‘‘አሃሃ! ልደትን ማክበር በሸሪዐው ከየት መጣ?’’ ልል ብዬ ሸኻቸው ማን እንደሆነ ሳስታውስ ተውኩት ። የምር ግን አባባ ቀረዷዊ (ፍሬንድ አታፍጥ! ‘‘አባባ’’ ያልኩት ዕድሜ ባለፀጋ ስለሆኑ ነው! አሁንም አታፍጥ! ሰማንያ ምናምን አመት ሞልቷቸው ‘‘ቀርዬ!’’ እያልኩ እንዳቆለጳጵሳቸው ፈልግክ እንዴ? ሆ! ምናለ አባባ ሲነኩ እንደምትፈርጠው የታላቁ ነቢያችን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሱና ሲነካ በፈረጥክ !? አረ መፍረጡንስ ተወውና ምነው ትንሽ… ትንሽዬ እንኳን ቅር ባለክ !? አስኮናኝ! ውይ..! ለካ ቅንፍ ውስጥ በቃ እሺ.. ልውጣ) ። እናማ አንዱ አድናቂ የምን አድናቂ አምላኪ እንጂ (ለምን ‘‘አምላኪ’’ እንዳልኩ እመለስበታለው) ምን ብሎ ፃፈ መሰላቹ ‘‘አላህዬ ቀረዷዊን በአይኔ ሳታሳየኝ አትግደለኝ’’ አለ ። ወቸው ጉድ! እኔማ ‘‘አይ! ግዴለህም ይሄ ነገር አይንህ ነው እንጂማ.. የሚለው ሌላ ነው’’ አልኩኝ ለራሴ ። ግን ድጋሚ ባነበው ለካ ያው ነው። (እንግዲህ ምን ይደረጋል ስሜት ልቦናን ሲጋርድ እንዲ ነው)
ቀረዷዊን (አላህ ሂዳያ ይስጠውና) ግብፅ የሚገኘው አል አዝሃር ዩኒቨርሲቲ ከተኮሰው ጊዜ ጀምሮ ይሄ ሰው በውኑ ነው በሕልሙ ‘ፈታዋ’ የሚሰጠው በሚያስብሉ ‘ብይኖቹ’ አለምን ሲያናጋ የነበረ እያናጋም ያለ አደገኛ ፍጡር ነው ።
ሰውየው ሶሪያ ከሚኖርበት ጊዜ ጀመሮ ታላቁ ሙሃዲስ ሸይኽ አልባኒ ረሒመሁላህ ያውቁት ኖሮ ይህን ፈላስፋ ማስጠንቀቅ የጀመሩት ገና ከረፋዱ ነበር ። ቀረዷዊ ግን ገፋበት ። የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰላም አሃዲሶችን በተጣመመ አስተሳሰቡ ልግዋም እንደተበጠሰበት ፈረሰኛ ጋለበበት ። አረረ! እንደውም ሃዲስ አልቀበልም እስከማለት ደረጃም ደርሷል ።
እናማ ይህ የዛሬው የሰማኒያ ምናምን አመት አባባ እስከዛሬም ድረስ ‘‘ተው’’ ቢባል ‘‘እምቢ!’’ ብሎ ግልቢያውን ተያይዞታል ። ቅድም ለሃረሪ ‘‘አረንጓዴ መብራት’’ ነው ያልነው ? ቀረዷዊ ግን አረንጓዴ ያንሰዋል! ። ከዛም አልፏል! ሰማያዊ እንበለው ይሁን? እሺ ‘‘ሰማያዊ መብራት’’ ። እናማ ይሄ ሰማያዊ መብራት አላህና መልዕክተኛው የተከለከለ (ሃራም) ያደረጉትን ነገራቶች የተፈቀደ (ሃላል) በማድረግ አቻም አልተገኘለት’ኮ እናንተየ’ዋ ። አላማው ምንድር ነው?
አላማው..? አላማውማ! አንተ እንዳትከፋበት ብሎም እንዳትርቀው ነው !
‹‹ይወድሃል!›› በጣም ነዋ! መውደድ እንዲ ከሆነ ከኡሚዬ የበለጠ ነዋ ለዛውም!
ዋናው አላማ ግን ማንንም ሰው ‹‹ሳያስከፋ›› ደጋፊ መሰብሰብ ከዚያም ከታች COMMENT መስጫ ቦታ ላይ የሚንጫጩትን አይነት ጭፍን ተከታዮችን ማፍራት ከዚያም….
ሰፈራችን መብራት ሳይሄድ የሰማያዊ መብራት ጉዶችን ልዘርዝራቸው ?
ከምን ልጀምር ? እሺ ቅድም ‘‘አስታውሰኝ’’ ያልኩክ ምን ነበር ? አዎ! እሱን..!
- ለጳጳሱ ከአላህ ምሕረት መጠየቅ ? ይቻላል
ቀረዷዊ የክርስትያኖቹ ቄስ የነበሩት ‘ባባ ቫቲካን’ ሕልፈተ-ሂወት አስመልክቶ ‘‘አላህ እዘንለት(ረሒመሁላህ) ’’ ይለናል ይሀው እራሳቹ ስሙት
https://www.youtube.com/watch?v=Oj_LjxcwQvA
አላህን እና መልዕክተኛውን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የሚሳደቡ እና የሚጠሉ ብሎም በአላህ ላይ የሚያጋሩ ከሃዲ ሰዎችን እንዴት ምህረት ይጠየቅላቸዋል??? ለዛውም ለቫቲካን ጳጳስ?
አላህ ሱብሃነሁ ወተዐላ ለታላቁ ነቢይ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሚወዱት አጎታቸው አቡ ጧሊብ ምንም እንኳን ለኢስላም ጥሩ ስራ ቢሰራም ምሕረትን ግን እንዲጠይቁለት አልፈቀደም ።
{ለነቢዩ እና ለነዛ ላመኑት ለአጋሪዎቹ የዝምድና ባለቤቶች ቢኾኑም እንኳ እነሱ (ከሃዲዎቹ) የእሳት ጓዶች መኾናቸው ከተገለፀላቸው በኋላ ምሕረትን ሊለምኑ የሚገባ አልነበረም} [አት-ተውባ - 113]
- በአላህ ላይ የካዱት ፣ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለምን ነቢይነት የማይቀበሉ ኢሳን የሚያመልኩ አላህን ልጅ አለው የሚሉ ቁርዓንን የማይቀበሉ የአሳማ ስጋ የሚበሉ አስካሪ መጠጥን የሚግቱ ጡሃራ የማያደርጉ ካፊሮች ‘‘ክርስቲያኖችን ወንድሞች’’ ማለት ይቻላል ይለናል ።
እንደውም ምን አለ መሰላቹ ‘‘ እኔ ‹‹ክርስቲያን ወንድሞቻችን›› ማለቴን የሚቃወሙ አሉ ። አላህ እኮ እንዲህ ብሏል ((አማኞች ወንድማማቾች ናቸው)) ። አዎ እኛም አማኞች ነን እነሱም በሌላ ወነን አማኞች ናቸው ። ስለዚህ ..’’ ብሎ ሊያብራራ ይዳክራል ።
አላሁ ሙስተዐን.. እኔ ምንም አልልም ግን አላህ መልስ ሰጥቶታል ። የዛሬ አንድ ሺህ ኣራት መቶ አመታት በፊት ያውም ።
(( በአላህና በመጨረሻው ቀን የሚያምኑትን ሕዝቦች፣ አላህንና መልክተኛውን የሚከራከሩትን ሰዎች፤ አባቶቻቸው ወይም ልጆቻቸው፤ ወይም ወንድሞቻቸው ወይም ዘመዶቻቸው ቢኾኑም እንኳ የሚወዳጁ ኾነው አታገኛቸውም፤ እነዛ በልቦቻቸው ውስጥ እምነትን ጽፏል፤ ከርሱም በኾነ መንፈስ ደግፏቸዋል፤ ከሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ ያገባቸዋል፤ አላህ ከነርሱ ወዷል። ከርሱም ወደዋል፤ እነዚያ የአላህ ሕዝቦች ናቸው፤ ንቁ የአላህ ሕዝቦች እነሱ ምኞታቸውን የሚያገኙ ናቸው)) [58:22]
- ሙዚቃ ከነመሳሪያው ይቻላል? በደንብ ነዋ! (አል ሃላል ወል ሃራም (በዚ ያቆማል ተብሎ ሲጠበቅ) በፈታዋ ሙዐሲራ ደገመው በሌሎቹም ኩቱቦቹ ይህንኑ ይደጋግመዋል) . ‘አርረ እንደውም እኔም እሰማለው ምን ታመጣላቹ?’ ብሎን እርፍ! እሽ እሱስ ይሁን ‪#‎ባንልም‬… የወንድ ሙዚቃ ቢሰማ ደግ ‪#‎አል_ነበር‬ ግን እሱ የነፋይዝዬ ፣ የነሻዲያዬ ፣ የነ ኡሙ ኩልሱም እና የነፌሩዝን ነው የሚኮመኩመው ። (አል-ረያን የተባለው የቃጣር መፅሄት የቁጥር (5969) ዕትም ላይ ‘ጉብ’ ብሎ ታገኙታላቹ)
አሁንም እኔ ምንም አልልም! ቃልም አይወጣኝ! ግን የአላህ መልዕክተኛ ምን ብለው ነበር መሰላቹ ?
‹‹ .. ከኔ ኡመት ሰዎች ይመጣሉ ለወንድ ልጅ ሀር ልብስን የሚፈቅዱ፤ መጠጥን እና የሙዚቃ መሳሪያን የሚፈቅዱ..›› ይሉናል አሽረፈል ኸልቅ
ሰደቀ ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይሀው ትንቢታቸውን በህይወት አድርሶን አየነው!
ቀረዷዊ በነኢማሙ ሻፊ ግዜ ቢኖርማ እንኳን ሙፍቲ ሊሆን እንደተራ ሰውም ምስክርነቱ ተቀባይነትም አያገኝ! አረረ እንደውም ‘ቂል’ ነበር የሚሉት ሂሂ!
ኢማሙ ሻፊ ረሒመሁላህ ‹‹ (ሴት ዘፋኝን) ዘፈንን የሚሰማ (سفيه )ቂል ነው ምስክርነቱም ተቀባይነት የለውም›› [الأم للشافعي ٦\٢٠٩]
- ግለ ወሲብ (ሴጋ) (Masturbation) ይቻላል ። (አል ሃላል ወል ሃራም)
ይቀፋል አይደል ? ምን ላድርግ ብላቹ ነው ። እናንተን ለማሳወቅ ስል ነው እንጂ ይሄንስ ጉድ መፃፍም ይደብራል ። ለማንኛውም ቀረዷዊ ‘‘ይቻላል’’ ይላል ። የረሱል አለይሂ ሰላቱ ወሰላም ይችን ሃዲስ በቃሉ ያላፈዘ ወንደላጤ አለ ለመሆኑ ?
‹‹እናንተ ወጣቶች ሆይ ማግባትን የቻላቹ አግቡ ፤ ያልተፈቀደልትን ከማየትና ዝሙት ላይ ከመውደቅ ይከለክለዋልና ፤ ያልቻለ ደሞ ይፁም ፤ ፆም ለእኩይ ጋሻ ይሆነዋልና›› (ሃዲሱ እዚጋ ያበቃል)
ቀረዷዊ ጋር ግን ሃዲሱ በዚ አላበቃም መሰል ሌላም አማራጭ አምጥቷል ለዛውም አፀያፊ !
አሁንም ኢማሙ ሻፊ መልስ ይስጡት..
ኢማሙ ሻፊ ግለ ወሲብ ሃራም ለመሆኑ ይሄን የቁር አን አያ ይጠቅሳሉ
(( ምእምናን ፍላጎታቸውን ሁሉ በእርግጥ አገኙ (ዳኑ)፡፡እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ውስጥ (አላህን) ፈሪዎች፡፡ እነዚያም እነርሱ ከውድቅ ንግግር ራቂዎች፡፡ እነዚያም እነርሱ ዘካን ሰጭዎች፡፡ እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የሆኑት (አገኙ)፡፡በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዟቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡ከዚህም ወዲያ የፈለጉ ሰዎች እነዚያ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ናቸው፡፡)) (ሱረቱ አል-ሙእሚኑን 1-7)
- ፊልም ይቻላልበወለድና በአራጣ ገንዘብ ቤት መስራት ይቻላል (አል-ሃላል ወል-ሃራም )
መልስ(2፡275)
- አጥፍቶ መጥፋት ይቻላል (Must Innocents Die? 19-28)
መልስ(4፡29)
-አስካሪ መጠጥ ትንሽ ፐርሰንት ይሁን እንጂ ችግር የለውም (አል-ሃላል ወል-ሃራም )
ብቻ ምን አለፋቹ ‘‘ይቻላል’’ በ ‘‘ይቻላል’’ የሆነ ሰማያዊ መብራት ነው ደክሞኝ እናንተን ላለማድከም ብዬ እንጂ ብዙ..ዙዙ መጥቀስ ይቻላል። ።
ጉደኛ የሆነ የፈታዋ መፅሃፍ አለው! ‹‹አል-ሃላል ወል-ሃራም›› የሚል እንደውም የሃገራችን ሰማያዊ መብራቱ ሃሰን ታጁ ከተረጎማቸው የቀረዳዊ መፅሃፎች አንዱ ነው ። አይ ሃሰን ታጁ !? እንደው እኔ ምለው ተረት ተረትኛ መፅሃፍ ቢተረጉም አይሻለውም ነበር ? ምነው! በግንባራቹ አትዩኝ! ። እና በዲን ጉዳይ ላይ የሚዘባርቀውን በሰማያዊ መብራት ይሄን ሕዝበ ሙስሊም ከሚያጠም ተረት መፅሃፍ ይሻል አልነበር? ። እናማ ወደ መፅሃፉ ስመጣላቹ ‹‹አል-ሃላል ወል-ሃራም›› የሚለውን መፅሃፍ አንድ ሸኽ ምን አሉት መሰላቹ ? ‘‘ይሄን መፅሃፍ ‹‹ አል-ሃላል ወል-ሃራም›› ከሚለው ‹‹አል-ሃላል ወል- ‪#‎ሃላል‬›› ቢለው ይሻል ነበር ” ።
ነገሩ እንዲህ እያለ ይሄ ሰውዬ አላህ ሃላል ያደርገውን ሃራም ሲያደርግ ሃራም ያደረገውን ሃላል ሲያደርግ የኢኽ ዋኑል ሙፍሲዲን ቦተሊከኞች ከስሜታቸው ጋር እንዲሄድላቸው ብሎ ባሳተመው መቶ ሃያ መፅሃፍ አይናቸውን ጋርዷቸው በግብዝ አፋቸውን ሞልተው ያቆለጳጵሱታል ይነዱለታል ።
(( ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን አንድን አምላክ ሊገዙ እንጂ ያልታዘዙ ሲኾኑ ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳታቸውን፣ የመርየምን ልጅ አልመሲሕንም ከአላህ ሌላ አማልክት አድርገው ያዙ፡፡))
የምትለው አያህ በወረደች ግዜ አንድ ለመልዕክተኛው ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም “እነርሱ እኮ ሊቃውንቶቻቸውንና መነኮሳታቸውን አማልክት አድርገው አልያዙም” አላቸው:: እርሳቸውም: “እንዴታ!” አሉት ፥ “ሀራሙን ሀላል ሀላሉን ሀራም አደረጉላቸው እነርሱም ተከተሏቸው ፥ ይህ ነው እነርሱን ማምለክ ማለት!”
እናማ ቀረዳዊን አጨብጫቢዎቹ አድናቆት ብቻ ሳይሆን አምልኮ ሊደርሱ ምን ቀራቸው? ወልኢያዙቢላህ
ወደ ሹመት ክፍል ስንገባ ምንም እንኳን ቀረዷዊ ልክ እንደ አብዬ አረንጓዴ መብራት ሃረሪ ጠጠር ያሉ ስሞች እስካሁን ባይሸለምም ግን ‘‘ማን ከማን ያንሳል!’’ የሚልበትን ያክል አላጣም..
ለምሳሌ ሁሌም ኢኽ ዋኖች (ይሄን ስማቹን ማትወዱት አላቹ አሉ እና ቆይ እኛ ምን እናድርግ ? ኢኽ ዋን ላይ የሚታዩ የኢኽቦላ ቫይረስ ምልክቶች ሁሉ ይታይባቿል ፤ ቀረዷዊን ማድነቅና ለሱ ጋሻ መሆን አንዱ የ ኢኽቦላ መገለጫ symptom ነው እህሳ? ) እናማ ኢኽዋኖች አውሮፓ ነው አሉ አዎ እንደውም አየርላንድ የሚባል የካፊር ሃገር ተሰባሰቡና ‹‹ የአውሮፓ ፈታዋና ሪሰርች ካውንስል መሪ›› ብለው መረጡት ። ከዚያስ .. ሰማያዊ መብራት በ2004 እ.ኤ.አ ቢጤዎቹን አሰባሰበና ቃጣር (ኳታር) ላይ ‹‹የዐለም›› (ልብ በል እዚጋ!) ‹‹ የዐለም ዑለማዎች ምክር ቤትን›› መሰረቱና ‹‹ሊቀመንበር›› አድርገው ሾሙት ።
አይ ኢኽ ዋኖች እንደው ከራስ በላይ ላሳር ናቸው እኮ! ። ትዝ ይላቿል የዛሬ ዐመት ነው ሁለት ዐመት ገደማ የኛዎቹ የአረንጓዴ መብራት ክብሪቶች ቀበሌ ተሰባስበው እርስ በርስ ሲመራረጡ? ከዚያማ ቲቪ ላይ ብቅ ብለው እንደውም ….
በቃ ልክ እንደነሱ ቀረዳዊም ‹‹ሊቀመንበር›› ሆነ! ። ማነው የዐለም ‹ዑለማ› ? መልስ የለም! ‘‘በቃ የዐለም ዑለማ ተብለካል የዐለም ዑለማ አርፈህ ቁጭ! ዝም! ጭጭ! በል!’’ ።
ወላሂ በሕይወቴ ግን እንደ ኢኽዋን መሰሪ አላየውም!!
ሲፈልጉ እላላላላላይ ማንም እንዳያወርድክ አድርገው ይሰቅሉካል ። ከፈለጉ ‘‘ጀነት ተመስክሮላካል!’’ ይሉካል ። ‘‘አኣ አኣ ወዴት ወዴት? ተውሒዱስ ሽርኩስ ሱናውስ ቢድዐውስ’’ ካልክ ግን ጉድህ ፈላ! ። አንተ ከሚስት ህና ከልጆችክ ጋር ቤትክ ቁጭ ብለክ እየተጫወትክ ‘‘እስራዒል ኤምባሲ አየነው’’ ይሉካል ። ‘‘አረረ ያለውት እዚው ነው! ብትል ማን ይሰማካል ? ’’ ሚዲያው በእጃቸው !። ፈላጭ ቆራጭ ናቸው ። ምንም የማያውቀውን አንገት ደፍቶ ኪታቡን አንጠልጥሎ ኡስታዙ ጋር ኢልም ፍለጋ !የሚሄድን እንቦቅጭላ አንድ ፍሬ ልጅ ገና ኡስታዙ ጋር ሳይደርስ መንገድ ላይ ይቀልቡትና ‹‹ የፖለቲካ ተንታኝ›› ያደርጉታል ። ‘‘ ቦርቀቅ በል! ’’ ነው በቃ ። ‘‘ ምን ትፈልጋለክ ሙዚቃ?’’ ‘‘ የሚፈቅድ ሸኽ አለን አብሽር!’’። ‘‘ የእነንትና ሃገር ሙስሊም መሪ አልተመቸክም ? ’’ ‘‘የሚያከፍር ሸኻችን ሞልቶን’’ ። ‘‘ሱሪ እና ፂም ልታሳጥር ? ’’ ‘‘አታደርገውም! ሸኽ ሃሰነል በና ሙሉውን መቼ አሳጠረና ? ከርክመው’’ ።
‘‘ እነ እንትና ሸኽ ግን ይሄን ነገር አይቻልም ሲሉ ሰምቼ..’’ ብለክ ሳትጨርስ ‘ኤጭ! አንተ ደሞ። እነሱ ጠርዘኞች ናቸው። ጠባብ አስተሳሰብ ያላቸው ናቸው። እንደውም ዋቂዑን (ተጨባጭ ነበራዊ ሁኔታ) አያውቁም።’’
ከፋፋይ ናቸው የንጉስ ቅጥረኛ
ምንም ማይገባቸው የኩርሲ ጠበቃ
አታክብድ አታክርር ሁሉም አለ ከኛ
ይሄ ነው መርሃችን ኢኽዋን ነው 1ኛ
(ትባላለህ)
(ወይ ጉድ! የት ገባው ሰዎች ? የነሱ ነገር ከተነሳ ማቆሚያም የለኝ'ኮ)
….
ለማንኛውም ስለ ሰማያዊ መብራት እንቀጥል ። አዲስ መስመር ላይ
እና ሰማያዊ መብራት ከ ‹‹ ሙፍቲ ፣ ረኢሱል አል ኢቲሃድ አልዐለሚ ሊዑለማኡል ሙስሊሚን ፣ እስከ ኢማም ሙዐሊፍ ፣ አል አላማ ፣ መጅሙዐት ሚን ሙአሊፋት ወአዕማል ዱክቶር ፣ አሸይኽ ዩሱፍ እያለ ሄዶ ሄዶ.. (በመጨረሻም) ቀረዷዊ›› ላይ ያበቃል።
የማልክዳቹ ነገር ሸኽየው ከስሜት ጋር የሚሄድ ፈታዋዎቹ ምቹና በተለያየ ሃገርኛ ቋንቋ አለም ላይ መፅሃፍቶቹ ስለተበተኑለት አድናቂዎቹ በርግጥ ብዙ ናቸው ። ግን ሰውየው ምንም አያውቅም! ። እኔ አይደለም ያልኩት ሸኽ አልባኒ ናቸው ። ግን አድናቂዎቹ ምን ይላሉ መስለክ ?
1) ሸኽ ቀረዳዊ መቶ ሃያ መፅሃፍት አሳትሟል ።
መልስ..
ቢቸከቸክ ቢቸከቸክ ምን ዋጋ አለው? ። ጠብ የሚል ነገር ከሌለ ? በመቶ ሃያ መፅሃፍት ውስጥ ከመቶ የሚበልጡ ቢድዐዎች የሚያጠሙት መቶ ሺሕ ሕዝብስ?
2) ሸኽ ቀረዳዊ ‹‹ የዐለም የኡለማዎች ምክር ቤት ሊቀመንበር›› ነው ።
መልስ..
እዚጋ ማስተካከያ አለ ። ‹‹ የዐለም የኡለማዎች›› ሳይሆን የዐለም ኢኽዋኖች በል ። እስኪ ኡለማዎች ካልካቸው ውስጥ ኪታቡን ያነበብክለት አንድ ሰው ጥራልኝ ? ኢኽዋኖች ተሰብስበው ለራሳቸው ሳያሳንሱ የቆረሱት ዳቦ ነው። አትሸወድ !
3) ቁርአን ሃፊዝ ነው እንደውም በልጅነቱ ነው አሉ የሀፈዘው ።
እና ምን ይሁን ? ዐብደላህ ሃረሪም እኮ ሃፊዝ ነው ። አላውቅም ነበር ብቻ እንዳትለኝ ። እና እሱንስ ቁርአን ስላፈዘ ትከተለዋለክ ? እንደውም ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ምን ይላሉ መሰለክ ? ‹‹ ወደፊት ሰዎች ይመጣሉ ቁርአንን ያነቡታል ግን ከጎሮርዋቸው አያልፍም›› ። ኡለማዎች ይሄም ሲፈስሩ ‹‹ ቁርአንን በቃላቸው ይሸመድዱታል ግን አይጠቀሙበትም›› ማለት ነው ይሉናል ።
ታዲያ ምን ተሻለህ ? ፂሙን እኮ ያሳድጋል ልትለኝ ነው? ። ደሞ ያሳድጋል ሳይሆን ይከረክመዋል በል ። እንደው ለፂምም ከሆነ የጓደናዬን ግጥም እዚጋ ልዋስልክ
▼ ያስተሳሰብ ክሕሎት ችሎታም ቢጎድላት ▼
▲ ለፂም ለፂምማ ውርዬም ፂም አላት ▲
________
አንድ ጓደኛዬ ✍
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናማ (ሆሆ! ስንተኛዬ ነው ይሄ ‘እናማ’ ? በቃ በዚ አበቃለው ይቺን ብቻ..) እናማ ቀረዷዊ ሚዲያውን (አልጀዚራና (የዐረብኛው) የመሳሰሉት) መፅሃፉን መፅሄቱን ራዲዮውን ተጠቅሞ ይሄን ጉዳ-ጉዱን በአራት አቅጣጫ ሲበትን ኡለማዎች (እነዚ ትክክለኛ ኡለማዎች ናቸው እንደነዛ ፌክ እንዳይመስሉክ እራሳቸውን ‹‹ሊቀመንበር›› ብለው አይመርጡም አያመራርጡምም) ዝም አላሉትም ።
ጭስ ጭስ ይሸተኛል ። ስማኝ ወንድሜ እኔ አንተን ለማስከፋት ብዬ አይደለም ይሄን የፃፍኩት ነገር ግን ከተሰጠህ የዕንቅልፍ ክኒን ሽለባ ትነቃ ዘንድ ነው ።
➤ ➥(የ)ምራቻ መንገድ ከተገለጠለት በኍላ መልዕክተኛውን የሚፃረርና ከሙዕሚኖች መንገድ ሌላ የሚከተል የመረጠውን (ጥመት) እናሸክመዋለን ፤ ጀሃነምም እናገባዋለን ፤ ከመመለሻነትዋ (አኳያ)ም የከፋች ሆነች። ➘➘↡
╔╔ ሱረቱ አል፡ኒሳእ 115 ╗╗
እንግዲያውስ ኡለማዎች ምን አሉት?
ከታላቁ የየመን የሱና አንበሳ ሙሃዲስ ሸኽ ሙቅቢል ረሒመሁላህ እንጀምር ?
- ሸኽ ሙቅቢል ረሒመሁላህ
‹‹ ቀረዷዊ ሆይ ከፈርሃልን (ክደሃልን?) ነው ወይንስ ለክህደት በጣሙን ቀርበሃልን ? ››
[ ነዝናዛውን ውሻ (ቀረዷዊን) ዝም ማስባል 110-112] በሚለው ኪታባቸው
- ሸኽ ዑሰይሚን ረሒመሁላህ አንድ ደርሳቸው ላይ ቀረዷዊ እንዲህ ያለበትን ንግግር በድምፅ አሰሟቸው
ንግግሩ ስለሚረዝም ዋናውን ቁጭ ላድርግላቹ.. ‹‹… አላህ እራሱን ምድር ላይ ተመራጭ (ምርጫ) አድርጎ እራሱ ቢመጣ ይሄን ያህል (99% ያመጣ ፕሬዝዳንትን እያደነቀ ነው) የምርጫ ድምፅ አያገኝም.. ››
ሸኽ ዑሰይሚን ረሂመሑላህ ምን አሉ መሰላቹ
‹‹ አዑዙቢላህ (በአላህ እጠበቃለው) ይህ ሰውዬ መቶበት ግዴታው ነው ። ካልቶበተ ግን ክዷልና (ከፍሯልና) መገደል ይገባዋል ። ምክንያቱም ፍጡርን ከፈጣሪ በላይ አዋቂ ስላደረገ ። በሱ ላይ ተውበት አለበት ። ከቶበተ አላህ ለባሮቹ ወንጀልን መሃሪ ነው ። ካልቶበተ ግን የሃገሩ ውላተል ዐምር (ንጉስ) አንገቱን በሰይፍ ብሎ ሊያስቆርጠው ይገባል..››
ይሀው ሙሉውን እራሳቹ ስሙት
https://www.youtube.com/watch?v=3DBGQKHoRIo
- ታላቁ ሙሃዲስ ናስሩዲን አል አልባኒ ረሒመሁላህ
‹‹.... የቀረዷዊ ፈታዋዎች ከሸሪዐ ይጋጫሉ ፤ ብዙ አደገኛ የፍልስፍና ሃሳቦችን ይሰነዝራል ፤ በሸሪዐው የተከለከሉ ድንጋጌዎች ላይ ሲመጣ ‘‘ይሄን የሚከለክል ግልፅ የሆነ ማስረጃ የለንም’’ ብሎ በዚህ ቃል ያጣጥላል ፤ ለዚህም ሙዚቃን የተፈቀደ ሃላል አድርጓል..››
https://www.youtube.com/watch?v=jKTka7j-d7o
እያለ ይቀጥላል የአሊም መዐት
ሸኽ አሕመድ ቢን የሕያ አል ነጅሚ ፣ ሸኽ ሙሀመድ ቢን ዐብዱላህ አል ኢማም ፣ አሕመድ መንሱር አል ዑደይኒ፣ ናስር ቢን ሃማድ አል ፋሃድ እና ሌሎችም …
(በዚህ ይብቃኝ.. ማይመለስ ከበረከተ የኔም ፅሁፍ ይቀጥላል)
ዋቢ መፃህፍት
ኢስካት ከልበል ዓዊ ሊ ሸኽ ሙቅቢን አል ዋዲ ረሒምሁላህ
አረድ አለል ቀረዷዊ ሊ ናስር ቢን ሃማድ አል ፋሃድ
_____
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን።
አላህ ሃቅን በሃቅነቱ እንዲያሳየን የምንቀበለውም እንዲያደርገን፤ ባጢልን በባጢልነቱ እንዲያሳየን የምንርቀውም እንዲያደርገን አላህን አለምነዋለሁ፡፡
አሚን አላሁመ አሚን

Post a Comment

0 Comments