Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ቃላቶቻችንን እንመዝን

ቃላቶቻችንን እንመዝን!
🔹ብዙ ሰዎች ባለማወቅ ወይም በጥንቃቄ ጉድለት የተለያዩ ከዲኑ ጋር የሚጋጩ ቃላቶችን ሲጠቀሙ ይስተዋላል:
ከነዚህም መሀል የተወሰኑትን ለምሳሌነት ስንመለከት፥
1/ አንድ በዲኑ ደካማ የሆነን ሙስሊም ሰው"ኢማንየለውም
አንበል")
ኢማን ከሌለው ካፊር ነውና! ካስፈለገም ("ኢማኑ ደካማ ነው") እንበል
2/ ዱኒያዊ ችግርና ከባድ ነገሮች ሲገጥሙን "ቂያማ ነው፣ ቂያማ ቆመ ወ.ዘ.ተ" አንበል
ቂያማ እንዲህ ቀላል አይደለምና! ጘይብ ከመሆኑ አንጻርም ምን እንደሚመስል አይታወቅምና
3/ ከሰላምታ በኋላ
ስለ ጤናና ቤተሰብ ስንጠይቅ
"ኢማን እንዴት ነው?" አንበል 
ተጠያቂ "ጥሩ ነው " ካለ እራስን የማጥራራት ችግር ላይ እንጥለዋለን!
💥ኢማን የለም ካለ ደግሞ ኩፍር ደረጃ ሊያደርስ የሚችል አደጋ ነው
4/ መጠሪያ ስማቸው
ያልሆነ ወንዶችን "ቢላል" ሴቶችን ደግሞ "ሱመያ" አንበል! 
የቱንም ያህል መልካም ስራ ቢሰራ ሰሓባ ያልሆነ ሰው የሰሓባን ደረጃ ሊደርስ አይችልምተራ ሰዎችን ከሰሓባዎች ማመሳሰል አላዋቂዎች መልካም ስራ ለመስራት የሞከረ ሁሉ የሰሓባ ደረጃ ያለው ሊመስላቸው ይችላል!
5/ አንድን ነገር ስንወስን ወይም ስንስማማ "አላህና አንተ/እገሌ ካለ" አንበልነገሮችን በሙሉ እንደፈለገ የሚያደርገው አላህ ብቻ ነው! ከርሱ ጋር አብሮ የሚወስን የለም የሰዎች ውሳኔም ከአላህ ውሳኔ በኋላ ነው!
6/ለአንድ ሰው ዱዓ
ስናደርግ መጨረሻ ላይ "ኢን ሻ`አላህ" አንበል  ሐዲስ ላይ ("አላህን ስትለምኑ በቁርጠኝነት ለምኑ!ከፈለክ ማረኝ / እንዲህ አድርግልኝ አትበሉ አላህን የሚያስገድደው የለም") ተብሏልና
7/የእርግማን ቃላቶችን ያለ ቦታቸው ከመጠቀም እንጠንቀቅ! በተለይም ከቤተሰብና ከህጻናት ጋር!
ብዙ ሰዎች ለምዶባቸው በየቀኑ የእርግማን ቃላቶችን በተለያየ መልኩ ይሰነዝራሉ ( ዓይን ይብላህ፣ገደል ግባ ፣ አፈር ብላ ወዘተ ዘግናኝና ፀያፍ የሆኑትም ሳይቀሩ ይሰማሉ
[ሙእሚንን መርገም ልክ እርሱን እንደመግደል ያክል ነው!]
💥("ቤተሰቦቻችሁ ላይ ዱዓ አታድርጉ! ዱዓችሁ የትኛው ሰዓት ላይ መቅቡል እንደሚሆን አታቁምና") ተብሏል።
8/ "እናትህ --" ይህ ሙስሊም ዘንድ አይደለም መናገሩ መጻፍና ማድመጡም እጅግ በጣም በጣም ይዘገንናል! ከመሆኑም ጋር ግን አልፎ አልፎ ሙስሊም የሚባሉም ጭምር ሲሉት ይሰማል! ይህ በራሱ ከባድና ውድቅ ቃል ከመሆኑም በተጨማሪ በዚህ መልኩ የሰውን እናት መስደብ የራስን እናት እንደመስደብ ነው! (ይህንንም ያሉት ነቢያችን ናቸው) ምክንያቱም የሰውን እናት የሰደበ የራሱን እናት ማሰደቡ አይቀርምና ነው!
9/ "እናቴ ትሙት አባቴ ይሙት" አይባልም
ምክንያቱም ይህ መኃላ ነው መማል የሚቻለው ደግሞ በአላህ፣በስሞቹና በመልካም ባህሪያቶቹ ብቻ ነው! ሐዲስ ላይም (ከአላህ ውጪ ባለ አካል የማለ ከፍሯል ወይም አሻርኳል ) ተብሏል
🔑ምላሳችንን እንጠብቅ!
🔑ቃላቶቻችንንም እንመዝን!
🔑ምላሱ ያልተስተካከለ ልቡ አይስተካከልም!
🔑 ልቡ ያልተስተካከል ደግሞ ኢማኑ አይስተካከልም!
✍ኡስታዝ አሕመድ ኣደም