Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ሠዎች በተለያየ ምክንያት ሀቅን አይቀበሉም


ሠዎች በተለያየ ምክንያት  አይቀበሉም በተፈጥሮ ነፍስ ጥሩ ጥሩ ነገር አያምራትም ነፍስያ ከተውሒድ ይልቅ
ሽርክ ከሡና ይልቅ ቢድአ እና ሁራፋት ከሀቅ ይልቅ ባጢል ባጢሉ ነው የሚያምራት.
☞ ነፍሢያ እና ሸይጣን የሠው.ልጆች ሀቁን አመዛዝነው ከመቀበል ፈንታ የተለያዩ ምክንያቶችን ሸልመው ሸላልመው ሀቅን እንዳይቀበሉ ያግዷቸዋል ከነዛ ውስጥ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው
① የቀደምት አባቶቻቸውን እና አያቶቻቸውን ተግባር ዛሬ ለሚሠሩት ውድቅ የሆነ ተግባር እንደ መረጃ በመጠቀም ከመጣላቸው ሀቅ ይሸሹበታል አላህ ይህን አስመልክቶ
እንዲህ ይላል «« እንደዚሁ በአንዲት ከተማ ውስጥ ካንተ በፊት መልዕክተኛን አላክንም። ተቀማጣዮቾ እኛ አባቶቻችንን በመንገድ ላይ አጊንተናል በነሡም ፋና
ተከታዬች ነን ያሉ ቢሆን እንጂ»
☞ ይህችንግግር ዛሬ አይደለም መባል የተጀመረችው ሆኖም ዛሬ ግን የቃሏ ይዘት.ምንም ሣይለወጥ የሚጠቀመው ሠው አለ ይህም እውነታውን ከመቀበል
ያግደዋል ።
② ለሠዎች ማንነት በልብ ውስጥ ትልቅ ቦታ መስጠት ፦ ዛሬ እጅጉኑ እየተንሠራፋ የመጣ ጉዳይ ቢኖር በሠዎች ላይ ድንበር ማለፍ ነው!! በሁለት አይነት መልኩ ሊታይ
ይችላል
1 ሠውን ከሚገባው በላይ ደረጃ ላይ ማስቀመጥ ይህም ሠውዬው የሚናገረውን ንግግር ያለምንም ማገናዘብ እና ማመዛዘን ከሠውዬው አፍ ስለወጣ ብቻ በጭፍን ለመቀበል ይዳርጋል!! ዛሬ ላይ እንደምናየው በየቦታው አሚር ቅቡርጥሤ እየተባለ ይሾማል የተናገረውን ንግግር ወይም ያዘዘውን ትእዛዝ ከሸሪአው አንግል ሣያይ አሚር ባለው አካል በመታዘዙ ብቻ አይኑን ጨፍኖ ይተገብራል
ከዛም ሀቁ ይህ ነው ስትለው የአሚር ትዛዝ ይልሀል!!!!
ም…ን ትለው ይሆን???? ልቀጥል …
2 ሌላው ተናጋሪውን ከልክ በላይ በመጥላት ብቻ የተናገረውን ንግግር ሣያደምጥ ጥቁር ይቀባውና የተናጋራው ማንነት ሀቁን እንዳይቀበል ተፅዕኖ
ይፈጥርበታል
☞ ግልፅ እንዲሆንላቹ ☞ ተውሒድን በማስተማር ኡማው ካለበት የሽርክ አዝቅት ለማውጣት ደፋቀና በሚሉ
ወንድሞቻችን የተለያዩ ስም በመለጣጠፍ የሚናገሩትን ሀቅ ተቀባይነት ለማሣጣት ይሞከራል እኔ ምመክርህ ምንም ናቸው ይበሉህ የውነት ሀቁን የምትፈልግ ከሆነ ወደ ሠውዬው ማንነት ሣይሆን ወደ ተናገረው ምንነት ተመልከት!!
አልይ ኢብኑ አቢጣሊብ. እንዲህ ሢል ይመክረናል ""ወደተናገረው ሠው ሣይሆን ወደተናገረው ንግግር ተመልከት """
③ በአላዋቂያን መመራት ፦ እምነት (ዲን) እንደመሆኑ መጠን የሚመራህ ሠው ማንነትን ጠንቅቀህ ልታውቅ
ይገባል አላህ እንዲህ ይላል ((እናንተ ያመናቹ ሆይ! ከሊቃወንታት እና ከመነኮሣት ብዙዎቹ በውሸት የሠዎችን
ገንዘብ. በርግጥ ይበላሉ ከአላህም መንገድ ያግዳሉ))
በአላዋቂ መመራት ተማሪ አስተማሪውን ስለሚመስል የአላዋቂ ባህሪን ይወርሣል ከጃሒል ባህራዎች አንዱ ሀቅን አለመቀበል ነው
④ ኩራት ፦ አላህ እንዲህ ይላል ((እነዚያን ያለ አግባቡ የሚኮሩትን ከአንቀፆቼ አዞራቸዋለው)) አላህ ያዞረውን ልብ በምንም አትመልሠውም ሞክረህው ከሆነ መልካም በሆነችዋ ስትከራከረው ይኮራል ይህ ደግሞ ጀነትን ህርም
ያደርግበታል.
☞ አንተ የአላህ ባርያ ሆይ ሌላ ሌላውን ተውና ራስህን ፈትሽበት!!!
አላህ ሆይ! እውነትን እውነት አድርገህ አሣየን
የምንከተለውም አድርገን!!!! —

አቡ ኢልሀም