Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ከሊቃውንቶቻችን አንደበት

by ustaz Jemal Yassin Abu Hamza
ߌከሊቃውንቶቻችን አንደበት
ኢማም አልበርባሀሪ ኣላህ ይዘንላቸውና " ሸርህ አል-ሱን'ና " በተሰኘው ኪታባቸው ውስጥ ባሰፈሩት ላይ እንዲህ ይላሉ
“ አንድ ሰው ከቢድዓ የሆነ ነገርን (ሲተገብር) በግልፅ ያሳየህ እንደሆነ፤ ተጠንቀቀው።
☞ ምክንያቱም ካንተ የሸሸገው (ቢድዓ) ግልፅ ካደረገልህ ይብሳልና።»
ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊም አላህ ይጠብቃቸውና ይህንን ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ :–
« የቢድዓ አራማጆችና ስሜታቸውን የሚከተሉ ሰዎች ራሳቸውን በመሸሸግና እንዳይደረስባቸው በመጠንቀቅ የታወቁ ናቸው።
~ የቢድዓ ሰዎች እምነታቸውንም ይሁን አካሄዳቸውን ሙሉውን ግሃድ አያደርጉልህም።
☞ የቢድዓ አራማጆች መርዛቸውን በጥቂት በጥቂቱ እንጂ አይሰጡህም።
ስለ ቢድዓ አራማጆች እንደሚባለው፤
" በቅድሚያ ስትገናኛቸው መርዛቸውን አይሰጡህም። ቀድመው የሚሰጡህ ማር ማሩን ነው።
~ በዚህም መልኩ ይሄድና ስትግባባው ይጋርድብሃል፤ ከዚያም ወደ ቢድዓው ይዘፍቀሃል።
~ ስለዚህ ከሆነ ሰው ላይ ቢድዓን በግልፅ ካገኘህ ጥንቃቄ አድርግ። ምክንያቱም የቢድዓ አራማጆች ሴረኞችና አታላዮች ናቸውና።»
ߓӡȝንጭ:
ዓውነል ባሪ (ገጽ 876)].
قال الإمام البربهاري في «شرح السنة»:
"وإذا ظهر لك من إنسانٍ شيءٌ من البدع فاحْذَره، فإن الذي أَخْفَى عنك أكثر مما أظهَر"
ߓԙ癄 الشيخ العلاّمة ربيع المدخلي:
"أهل البدع والأهواء معروفون بالتستر والتَّقِيّة، أهل البدع لا يُظهِرون لك كل شيءٍ من عقائدهم ومناهجهم، فالمبتدع يُعطيك شيئًا فشيئًا، كما قِيل عن أهل البدع إنه لا يُطعِمُك السم من أول جلسة، وإنما يُطعِمُك العسل أولاً، وهكذا حتى إذا أَنِسْتَ إليه دَسَّ سمومه عليك، ولبّس عليك، وأدخَلَك في بدعته. فإذا ظهر لك شيءٌ من البدع عند أحد فخُذ حذرك منه، فإنهم أهل مكر وأهل خِدَاع" .
[عون الباري ص٨٧٦]