Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

1.5 ቢልዬን ሙስሊሞች የአላህ መልክተኛ ነው ብለው የሚከተሉትን ውድ ሰው መንካት ፍትሃዊነት አይደለም

1.5 ቢልዬን ሙስሊሞች የአላህ መልክተኛ ነው ብለው የሚከተሉትን ውድ ሰው መንካት ፍትሃዊነት አይደለም፡፡ የነብያት ሁሉ ሃይማኖት ኢስላም አደለም የነብያትን ሁሉ ምርጥ አላህ የላካቸውን አንዱንም መልክተኛ ባለጊዎች እንዲነኩ፤ እንዲያነውሩ የፍጡራን ፈጣሪ አይፈቅድም፡፡
የአላህ መልክተኛን ﷺ የመረጣቸው አላህ ስለሆነ ባለጌዎች የሰሩትን ቢሰሩ እሳቸውን አይጎዳቸውም፡፡
በኢስላም እውቀት ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ሸሪዐን ሳይገጥም የሚሰራ ስራ ሰውየው ጥሩ አስቦ ቢሰራውም እራሱን እና ሙስሊሞችን የሚጎዳ ስራ መስራት ጥፋት ነው፡፡
ኢስላም ጥቅም እና ጉዳትን የሚመዝን ሃይማኖት ነው፡፡ ለካሃዲያን መልስ እሰጣለሁ ብሎ ሸሪዓን የሚጋጭ ነገር መስራት ወይንም መስፈርቱን ያላሟላ ስራ መተግበር መጨረሻው ጥፋት ነው፡፡
የሚወሰደው እርምጃ የባሰ ጥፋት እና መከራ ሙስሊሞች ላይ የሚያመጣ ከሆነ የባሰ ጥፋት ነው፡፡
አላህ በእውቀት ከሚንቀሳቀሱት ያድርገን፡፡

Post a Comment

0 Comments