Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

10ሩ ኢስላምን የሚያበላሹ ነገሮች







ኢስላምን የሚያበላሹ ነገሮች- አንተ ሙስሊም ወንድም ሆይ! እጅግ በጣም ብዙኢስላምን የሚያበላሹ ነገሮች እንዳሉ ልታውቅ ይገባሀል፡፡ ብዙ ጊዜ የሚከሰቱት አስር ያህሉ ሲሆኑ ልትጠነቀቃቸው ይገባል፡፡ እነርሱም፡-

አንደኛ፦ በአምልኮ ላይ ከአላህ ጋር ሌላን ማጋራት፡፡ አላህ y እንዲህ ይላል፡- -«…እነሆ!በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን(ጀነትን) በእርግጥ እርም አደረገ። መኖሪያውም እሳት ናት። ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም።» {አል-ማኢዳ ፡72} እዚህ አይነቱ ማጋራት ውስጥ ከሚካተቱ ነገሮች መካከል ሙታንን መለመን፣ከጭንቅ አውጡኝ (ድረሱልኝ)ማለት፣ለእነርሱ መሳል እና ማረድ ናቸው፡፡-«…እነሆ!በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን(ጀነትን) በእርግጥ እርም አደረገ። መኖሪያውም እሳት ናት። ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም።» {አል-ማኢዳ ፡72}እዚህ አይነቱ ማጋራት ውስጥ ከሚካተቱ ነገሮች መካከል ሙታንን መለመን፣ከጭንቅ አውጡኝ (ድረሱልኝ)ማለት፣ለእነርሱ መሳል እና ማረድ ናቸው፡፡
ሁለተኛ፦ አንድ ሰው በእርሱና በአላህ መካከል (ከፍጡራን)የሚማፀናቸውን፣ አማልዱኝ የሚላቸውን እና የሚመካባቸውን አማካይ ካደረገ በዑለማዎች ሙሉ ስምምነት (ኢጅማዕ) መሰረት ከኢስላም ይወጣል፡፡
ሶስተኛ፦ ከአላህ ውጪ ሌላን የሚያመልኩ ወገኖች (ሙሽሪኮች) ከሀዲያን (ካፊሮች) መሆናቸውን ያላመነ ወይም የተጠራጠረ አልያም አካሄዳቸው ትክክል ነው ያለ ሰው ከኢስላም ወጥቷል፡፡ 
አራተኛ፦ ከነብዩ (صلى الله عليه وسلم) መመሪያ ውጪ ሌላን መመሪያ ይበልጥ የተሟላ መሆኑንወይም ከእርሳቸው ፍርድ ይልቅ የሌሎች ፍርድ የተሻለ እንደሆነ ያመነ ሰው ከሀዲ ነው፡፡ እዚህ ውስጥከሚካተቱ ሌሎች ነጥቦች መካከል፦
ሀ. የተለያዩ ሰዎች የደነገጓቸው ሕግጋት እና የቀረጿቸው ስርዓቶች ከ ኢስላማዊው የሸሪዓ ድርጋጌዎች እና ስርዓቶችየተሻሉ ናቸው ብሎ ማመን፣ * ወይም ኢስላማዊው ስርዓት (ከተለያዩ ነገሮች አንፃር) በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ተግባራዊ ሊሆን አይችልም ብሎ ማመን፣ * ወይም ለሙስሊሞች ኋላቀርነት ምክንያቱ ኢስላም ነው ብሎ ማመን፣ * አልያም ኢስላም በግለሰብ እና በጌታው መካከል ባለ ግንኙነት ላይ የተገደበስለሆነ ሌሎች የሕይወት መስኮችን የሚመለከት አይደለም ብሎ ማመን፡፡ ለ.(እጅን ሊያስቆርጥ በሚችል ስርቆት ላይ የተገኘን ሰው) እጅን እንደ መቁረጥ ወይም ከጋብቻ በኋላ ዝሙት ላይ የወደቀን ሰው በድንጋይ መውገር ያሉ ኢስላማዊ የቅጣት ህግጋትን (ሊፈፅሙ በሚችሉባቸው አገራት)ተግባራዊ ማድረግ ካለንበት ዘመን ጋር የሚሄድ አይደለም ብሎ መናገር፡፡ ሐ. ሸሪዓዊ በሆኑ ማህበራዊ ግንኝነቶች(ሙዓመላት) ወይም የቅጣት ህግጋት አልያም ከዚያ ውጭ በሆኑ ጉዳዮች አላህ ካወረደው ሕግ ውጭ በሌላ መፍረድ ይቻላል ብሎ ማመን፡፡ ምንም እንኳ ግለሰቡ እነዚያን (አላህ ካወረደው ውጭ ያሉ ሕግጋት) ከሸሪዓዊው ፍርድ ይሻላሉ ባይልም (ይህ እምነቱ) ክህደት ውስጥ ይከተዋል፡፡ ምክንያቱም በሁሉም ዑለማዎች ስምምነት (ኢጅማዕ) መሰረት ግለሰቡ ይህንን በማመኑ አላህ እርም ያደረጋቸውን ይፈቀዳሉ እንዳለ ነውና የሚቆጠረው፡፡ አላህ እርም ያደረጋቸውን እንደ ዝሙት፣አስካሪ ነገሮችን መውሰድ፣ ወለድን መጠቃቀም እና ከሸሪዓ ውጭ ባለመፍረድ ያሉበኢስላም እርምነታቸው ግልፅ የሆኑ ጉዳዮች ይፈቀዳሉ ብሎ ያመነ በአጠቃለይ የሙስሊሞች ስምምነት (ኢጅማዕ)መሰረት ካፊር ነው፡፡  
አምስተኛ፦መልዕክተኛው (صلى الله عليه وسلم) ከአላህ ይዘው ካመጡት መልዕክት ቅንጣት ታክል አንኳ ብትሆን ከድንጋጌነቱ አንፃር የጠላ ሰው ቢሰራበትም ከኢስላም ይወጣል፡፡ ይህ የአላህ ቃል እንደሚከተለው ይገልፀዋል፡- ፦ «ይህ እነርሱ አላህ ያወረደውን ስለጠሉ ነው፡፡ ስለዚህ ሥራዎቻቸውን አበላሸባቸው፡፡» {ሙህመድ ፡9} ሀ. የተለያዩ ሰዎች የደነገጓቸው ሕግጋት እና የቀረጿቸው ስርዓቶች ከ ኢስላማዊው የሸሪዓ ድርጋጌዎች እና ስርዓቶችየተሻሉ ናቸው ብሎ ማመን፣ * ወይም ኢስላማዊው ስርዓት (ከተለያዩ ነገሮች አንፃር) በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ተግባራዊ ሊሆን አይችልም ብሎ ማመን፣ * ወይም ለሙስሊሞች ኋላቀርነት ምክንያቱ ኢስላም ነው ብሎ ማመን፣ * አልያም ኢስላም በግለሰብ እና በጌታው መካከል ባለ ግንኙነት ላይ የተገደበስለሆነ ሌሎች የሕይወት መስኮችን የሚመለከት አይደለም ብሎ ማመን፡፡* ወይም ኢስላማዊው ስርዓት (ከተለያዩ ነገሮች አንፃር) በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ተግባራዊ ሊሆን አይችልም ብሎ ማመን፣* ወይም ለሙስሊሞች ኋላቀርነት ምክንያቱ ኢስላም ነው ብሎ ማመን፣* አልያም ኢስላም በግለሰብ እና በጌታው መካከል ባለ ግንኙነት ላይ የተገደበስለሆነ ሌሎች የሕይወት መስኮችን የሚመለከት አይደለም ብሎ ማመን፡፡ለ.(እጅን ሊያስቆርጥ በሚችል ስርቆት ላይ የተገኘን ሰው) እጅን እንደ መቁረጥ ወይም ከጋብቻ በኋላ ዝሙት ላይ የወደቀን ሰው በድንጋይ መውገር ያሉ ኢስላማዊ የቅጣት ህግጋትን (ሊፈፅሙ በሚችሉባቸው አገራት)ተግባራዊ ማድረግ ካለንበት ዘመን ጋር የሚሄድ አይደለም ብሎ መናገር፡፡ሐ. ሸሪዓዊ በሆኑ ማህበራዊ ግንኝነቶች(ሙዓመላት) ወይም የቅጣት ህግጋት አልያም ከዚያ ውጭ በሆኑ ጉዳዮች አላህ ካወረደው ሕግ ውጭ በሌላ መፍረድ ይቻላል ብሎ ማመን፡፡ ምንም እንኳ ግለሰቡ እነዚያን (አላህ ካወረደው ውጭ ያሉ ሕግጋት) ከሸሪዓዊው ፍርድ ይሻላሉ ባይልም (ይህ እምነቱ) ክህደት ውስጥ ይከተዋል፡፡ ምክንያቱም በሁሉም ዑለማዎች ስምምነት (ኢጅማዕ) መሰረት ግለሰቡ ይህንን በማመኑ አላህ እርም ያደረጋቸውን ይፈቀዳሉ እንዳለ ነውና የሚቆጠረው፡፡ አላህ እርም ያደረጋቸውን እንደ ዝሙት፣አስካሪ ነገሮችን መውሰድ፣ ወለድን መጠቃቀም እና ከሸሪዓ ውጭ ባለመፍረድ ያሉበኢስላም እርምነታቸው ግልፅ የሆኑ ጉዳዮች ይፈቀዳሉ ብሎ ያመነ በአጠቃለይ የሙስሊሞች ስምምነት (ኢጅማዕ)መሰረት ካፊር ነው፡፡  
ስድስተኛ፦በአላህ ወይም በመፀሀፉ፣ በመልዕክተኛው () አልያም ከአላህ ዲን መገለጫዎች በአንዱየተሳለቀ (ያላገጠ) በእርግጥ ከኢስላም ወጥቷል፡፡ ይህም አላህ እንዲህ ስላለ ነው፡- ፦ «…በአላህና በአንቀጾቹ፣ በመልክተኛውም ታላግጡ ነበራችሁን?» በላቸው። አታመካኙ፣ ካመናችሁም በኋላ በእርግጥ ካዳችሁ።…» {አተውባህ ፡65-66} 
ሰባተኛ፦ድግምት መስራት ወይም ማሰራት ከዚሁ የሚካተተው "ሰርፍ" በመባል የሚታወቀው እና አንድ ግለሰብ ለሚስቱ ያለውን ፍቅር አስረስቶ እንዲጠላት ማድረግን መሰረት ያደረገ ተግባር ነው፡፡ በአንፃሩም "አል-ዐጥፍ" (መስተፋቅር) በመባል የሚታወቀው እና ሰይጣናዊ በሆነ መንገድ አንድን ሰው የማይወደውን እና የማይፈልገውን ነገር እንዲወደውና እና እንዲፈለገው የማድረግ ተግባር እዚሁ ውስጥ የሚጠቃለል ይሆናል፡፡ በዚህ አይነቱ ስራ የተሰማራ አልያም ድርጊቱን የወደደው ሰው በእርግጥ ከኢስላም ወጥቷል፡፡ ይህም ቀጣዩን የአላህ ንግግር መሠረት ያደረገ ነው፡- ትርጉሙም:- «…«እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ» እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም። …» {አል-በቀራ፡102} ማለት ነው። 
ስምንተኛ፦ በሙስሊሞች ላይ (የበላይነትን እንዲያገኙ)አጋሪዎችን (ከሀዲያንን) መርዳትና መተባበር። አላህ (عزوجل) አንዲህ ይላል፡- ፡- «…ከናንተም ውስጥ ረዳቶች የሚያደርጋቸው ሰው እርሱ ከነርሱ ነው። አላህ (ከሀዲያንን ረዳት እና ወዳጅ አድርገው የሚይዙ) አመጸኞችን ህዝቦች አያቀናም።» {አል-ማኢዳ ፡51} 
ዘጠነኛ፦ አንዳንድ ሰዎች ከመልዕክተኛው ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم) ሸሪዓ ስርዓት ውጪ መሆን ይፈቀድላቸዋል ብሎ ያመነ ሰው ካፊር ነው፡፡ አላህ እንዲህ ብሏልና፡-: ፡- «ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም። እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው።» {አሊ-ዒምራን ፡85}ማለት ነው። 
አስረኛ፦ ኢስላምን አልያም እርሱን በማወቅ እና ተግባራዊ በማድረግ እንጂ ኢስላም ሊረጋገጥ የማይችልባቸውን አንኳር ጉዳዮች ላለመማር እንዲሁም ገቢራዊ ላለማድረግ መሸሽ ከኢስላም ያስወጣል፡፡ ይህም አላህ (عزوجل) እንዲህ ያለ በመሆኑ ነው፡- ፡- «በጌታውም አንቀጾች ከተገሰጸና ከዚያም ከተዋት (ችላ ካለ) ሰው ይበልጥ በደለኛ ማነው? (የለም)፤ እኛ ከተንኮለኞቹ ተበቃዮች ነን፡፡»{አሰጅዳህ ፡22} ፡- «…እነዚያ የካዱትም ከተስፈራሩት ነገር(ችላ ብለው)ዘዋሪዎች ናቸው፡፡»{አል-አሕቃፍ ፡3} - እነዚህን ኢስላምን የሚያፈርሱ ነገሮች በተመለከተ ተገዶ ከሚፈፅማቸው ሰው ውጭ በቀልድ መልኩ፣ ሆን ብሎ እና(አደጋ ሊደርስብኝ ይችላል በሚል ተጨባጭ ያልሆነ) ስጋትበሚፈፅማቸው መካከል ልዩነት የለም፡፡ - የአላህን አሳማሚ ቅጣት እና ቁጣ ከሚያስከትሉ ነገሮች ሁሉ በእርሱ እንጠበቃለን፡፡፦ «…በአላህና በአንቀጾቹ፣ በመልክተኛውም ታላግጡ ነበራችሁን?» በላቸው። አታመካኙ፣ ካመናችሁም በኋላ በእርግጥ ካዳችሁ።…» {አተውባህ ፡65-66}

Sultan Khedir