Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ለእየሱስ ባሪያዎች!! የኢብኑል ቀይም አልጀውዚያህ ድንቅ ግጥም ግርድፍ ትርጉም በኢብኑ ሙነወር


ለእየሱስ ባሪያዎች‼️
===============
የመሲህ ባሮች ሆይ አንድ ጥያቄ አለን
የተረዳው ካለ መልሱን እንሻለን
ጌታ ግፍ አቅቶት ሰዎች ከገደሉት
አለቀ አከተመ የታል አምላክነት?!
ሰዎች የሰሩትን በሱ ላይ ሲያደርሱ
ጌታ ግብራቸውን ፈቅዶ ነው በራሱ?
እንዲያ ከሆነማ ምንኛ ታደሉ?!
ፍቅሩን ይቸራሉ ፈቃዱን ሲሞሉ::
ባደረሱት ሁሉ አልፎ ከተከፋ
እንግዲህ ምን ይባል?
ሀይሉ ከኮሰሰ ሀይላቸው ከሰፋ?!
ግን እንጠይቃለን ለመልስ አትንፈጉ
ማለባበስ ይቅር ይመለስ በወጉ
ፈጣሪዋን አጥታ ዐለም ስትዋትት
ሰው ወደ ማን ነበር የሚያስበው ፀሎት?
ፍጡር ፈጣሪውን ካፈር ሲያደባየው
ሰባቱን ሰማያት ማነበር ያቆየው?
ምስማር ተቸንክሮ ሲያሸልብ ፈጣሪ
ዓለም ቀርታ ነበር ያለ አስተናባሪ?
የሰማይ መላእክት ምንኛ ለገሙ?!
እጁ ተቸንክሮ ዋይታውን ሲሰሙ?
እንጨቱም ታምር ነው አቅሙ መቋቋሙ
አምላክ ያክል ነገር ችሎ መሸከሙ
ስለቱስ ጭቃኔው ብረቱ ምስማሩ
አካሉን ሰንጥቆ ስቃይ ማሳደሩ
ጉድ በሉ እሄን ጌታ በአይሁድ የሚረታ
ማጅራቱን ታንቆ ታስሮ የሚመታ
ኋላስ ራሱ ነቃ ከሞት አንሰራራ
ወይስ ጌታ አገኘ ህይወት የሚዘራ?!
ጉድ በሉ ለቀብር ጌታ አቅፎ ለያዘ
የባሰም ሆድ አለ አምላክ ያረገዘ
ዘጠኝ ወር ታሽጎ ሲኖር በጨለማ
ሐይድ እየተጋተ ደም እየተጠማ
ብልት ቀዶ ወጣ አቡሻ ህፃኑ
አፉን ለጡት ከፍቶ አቤት ማሳዘኑ!
አስቡ እሄን አምላክ ሲጠጣ ሲበላ
ከዚያም ያስገባውን ሲያስወጣ በሌላ
ጌታዬ ከፍ አለ ከነሳራ ቅጥፈት
ሁሉም ይጠየቃል ለቀባጠረበት
የመስቀል ባሮች ሆይ ግራ ገባኝ እኔ
ያሽቀነጠረው ሰው ፅድቅ ነው ኩነኔ
ማቃጠል ሰባብሮ ፈቃጁን ጨምሮ
ህሊና ከዚህ ውጭ ይፈርዳል አምርሮ?
አምላክ አቅም አንሶት ለተጠፈረበት
ሰብሮ እንደማቃጠል ጭራሹን አምሎኮት?!
እውነትም እርጉም ነው ለምንስ ይዘንጋ
በመሳለም ሳይሆን በእግር ይሰጥ ዋጋ!
ለተዋረደበት ጌታህ ከነነፍሱ
አንተ ካመለከው የሱ ነህ የነሱ?
‘ጌታን ስላዘለ’ ከሆነ አክብሮቱ
አስተዋሽ ቅርፃቅርፅ ቢሆን እንጂ እንጨቱ
መስቀሉ ከጠፋ ሺ ስንት አመታቱ?!
እንዲያ ከሆነማ ሂሳቡ ቀመሩ
ለመስገድ አትቦዝን ለየመቃብሩ
ያስታውሳልና ነገረ ስርኣቱ
ጌታህ ካፈር በታች ለነበረበቱ::
የመሲህ ባሪያ ሆይ ንቃ ተረጋጋ
ይሄ ነው እውነታው ካልፋ እስከ ኦሜጋ፡፡
።።።።
የኢብኑል ቀይም አልጀውዚያህ “አዑባደል መሲሒ ለና ሱኣሉን” ድንቅ ግጥም ግርድፍ ትርጉም፡፡ ግጥሙን “ኢጋሠቱል ለህፋን ኪታክ ገፅ: 2/290 ላይ ያገኙታል፡፡

Post a Comment

0 Comments