Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

መንሀጀ ሰለፍ ላይ መፅናት እና ለፅናት የሚያግዙን ነገሮች

በመንሀጀ ሰለፍ ላይ መፅናት እና ለፅናት የሚያግዙን ነገሮች
(("ፅናት" ማለት በሀቅ ላይ ቀጥ መለት ነው።
"መንሀጅ" ማለት ሙስሊም የሆነ ሰው የሚጓዝበት መንገድ ነው።
እሱም ቀጥተኛው መንገድ ነው።
ﻗﺎﻝ ﺗﺒﺎﺭﻙ ﻭﺗﻌﺎﻟﻰ : { ﻗُﻞْ ﻫَﺬِﻩِ ﺳَﺒِﻴﻠِﻲ ﺃَﺩْﻋُﻮ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻋَﻠَﻰ ﺑَﺼِﻴﺮَﺓٍ ﺃَﻧَﺎ ﻭَﻣَﻦِ ﺍﺗَّﺒَﻌَﻨِﻲ ﻭَﺳُﺒْﺤَﺎﻥَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻣَﺎ ﺃَﻧَﺎ ﻣِﻦَ ﺍﻟْﻤُﺸْﺮِﻛِﻴﻦَ } ( ﻳﻮﺳﻒ 108: )
አላህ እንዲህ ይላል:-"ይህቺ መንገዴ ናት። ወደአላህ እጣራለሁ እኔም የተከተለኝም ሰው በግልፅ ማስረጃ ላይ ነን። ጥራት ለአላህ ይገባው። እኔም ከአጋሪዎች አይደለሁም" በል። ዩሱፍ 108))
በሀቅ ላይ እስከለተ ሞታችን ድረስ መፅናት በጣም አሳሳቢ ነው የመጨረሻችን ነገር ሊያሳስበን ሊያስጨንቀን ይገባል ለዚህም ሶላት በሰገድን ቁጥር "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" በማለት በቀጥተኛው መንገድላይ ፅናት እንዲሰጠን መማፀን ተደንግጎልናል
ﻗﺎﻝ ﺍﺑﻦ ﺗﻴﻤﻴﺔ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ : “ ﻭﻟﻬﺬﺍ ﻛﺎﻥ ﺃﻧﻔﻊ ﺍﻟﺪﻋﺎﺀ، ﻭﺃﻋﻈﻤﻪ ﻭﺃﺣﻜﻤﻪ ﺩﻋﺎﺀ ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ : { ﺍﻫﺪِﻧَﺎ ﺍﻟﺼِّﺮَﺍﻁَ ﺍﻟﻤُﺴﺘَﻘِﻴﻢَ ﺻِﺮَﺍﻁَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺃَﻧﻌَﻤﺖَ ﻋَﻠَﻴﻬِﻢْ ﻏَﻴﺮِ ﺍﻟﻤَﻐﻀُﻮﺏِ ﻋَﻠَﻴﻬِﻢْ ﻭَﻻَ ﺍﻟﻀَّﺎﻟِّﻴﻦَ
} [ ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ 6: ، 7 ] ، ﻓﺈﻧﻪ ﺇﺫﺍ ﻫﺪﺍﻩ ﻫﺬﺍ ﺍﻟﺼﺮﺍﻁ ﺃﻋﺎﻧﻪ ﻋﻠﻰ ﻃﺎﻋﺘﻪ ﻭﺗﺮﻙ ﻣﻌﺼﻴﺘﻪ، ﻓﻠﻢ ﻳﺼﺒﻪ ﺷﺮ، ﻻ ﻓﻲ ﺍﻟﺪﻧﻴﺎ ﻭﻻ ﻓﻲ ﺍﻵﺧﺮﺓ
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይምያ አላህ ይዘንለዎት እና እንዲህ ይላአሉ"ለዚህም ሲባል ጠቃሚ እና ጥቅል እንዲሁም ትልቅ ዱአ የፋቲሀ ዱአ ነው 'ቀጥተኛውን መንገድ ምራን የእነዚያን በነሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ' (ምራን በሉ)። (ፋቲሀ 6-7)
እሱ (አላህ ባሪያን) እሄን መንገድ ከመራው እሱን በመታዘዝ እና እሱን ማመፅን በመተው ላይ አገዘው በዱኒያም ይሁን በአኼራ ሸር(ተንኮል) አያገኘውም" መጅሙኡል ፈታዋ 14/320—321
በዲን ላይ መፅናት የነብዮች ኑዛዜ ነው።
ﻗﺎﻝ ﺗﻌﺎﻟﻰ : { ﻭَﻭَﺻَّﻰ ﺑِﻬَﺎ ﺇِﺑْﺮَﺍﻫِﻴﻢُ ﺑَﻨِﻴﻪِ ﻭَﻳَﻌْﻘُﻮﺏُ ﻳَﺎ ﺑَﻨِﻲَّ ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﺍﺻْﻄَﻔَﻰ ﻟَﻜُﻢُ ﺍﻟﺪِّﻳﻦَ ﻓَﻼ ﺗَﻤُﻮﺗُﻦَّ ﺇِﻟَّﺎ ﻭَﺃَﻧْﺘُﻢْ ﻣُﺴْﻠِﻤُﻮﻥَ } ( ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ 132: )
"በርሷ (በህግጋቲቱ) እብራሂም ልጆቹን አዘዘ የእቁብም (እንደዚሁ ልጆቹን አዘዘ) ልጆቸ ሆይ! አላህ ለናንተ ሀይማኖትመረጠ ስለዚህ እናንተ ሙስሊሞች ሁናችሁ እንጅ አትሙቱ" አላቸው
በሀቅ ላይ ለመፅናት የሚረዱን ነገሮች
1)ኢማንን ማረጋገጥ
2)መልካም ስራ
3)በእውነት ላይ አደራ መባባል
4)በትእግስት ላይ አደራ መባባል
ለነዚህ ሁሉ መረጃው የአላህ ቃል ነው።
{ ﻭَﺍﻟْﻌَﺼْﺮِ . ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﺄِﻧْﺴَﺎﻥَ ﻟَﻔِﻲ ﺧُﺴْﺮٍ . ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻭَﻋَﻤِﻠُﻮﺍ ﺍﻟﺼَّﺎﻟِﺤَﺎﺕِ ﻭَﺗَﻮَﺍﺻَﻮْﺍ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﺗَﻮَﺍﺻَﻮْﺍ ﺑِﺎﻟﺼَّﺒْﺮِ}
"በግዚያት እምላለሁ። ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው። እነዚያ ያመኑት እና መልካሞችን የሰሩት፣በመታገስም አደራ የተባባሉት ሲቀሩ።"
አሁንም በዚህ ላይ የአላህ ቃል መረጃ ነው።
"አላህ እነዚያን ያመኑትን በቅርቢቱም ሕይወት በመጨረሻይቱም (በመቃብር) በተረጋገጠው ቃል ላይ ያረጋቸዋል ከሀዴዎችንም አላህ ያሳስታቸዋል አላህም የሚሻውን ይሰራል።" [ኢብራሂም(26)]
አሁንም በዚህላይ የአላህ ቃል መረጃ ይሆናል
: { ﻭَﺍﺳْﺘَﻌِﻴﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﺼَّﺒْﺮِ ﻭَﺍﻟﺼَّﻼﺓِ ﻭَﺇِﻧَّﻬَﺎ ﻟَﻜَﺒِﻴﺮَﺓٌ ﺇِﻟَّﺎ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟْﺨَﺎﺷِﻌِﻴﻦَ } ( ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ 45
"በመታገስ እና በሶላት ተረዱ እሩሷም (ሶላት) በፈሪይዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት።"
እውነተኛ በሆነ መንሀጅ ላይ መፅናት የአህሉሱናዎች ባህሪ ነው።
በዲን ላይ መገለባበጥ እና ሀቅ በሆነ መንሀጅ ላይ አለመፅናት የአህሉል ቢደእ ባህሪ ነው
ﻗﺎﻝ ﺍﺑﻦ ﺗﻴﻤﻴﺔ ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ : “ ﺇﻧﻚ ﺗﺠﺪ ﺃﻫﻞ ﺍﻟﻜﻼﻡ ﺃﻛﺜﺮ ﺍﻟﻨﺎﺱ ﺍﻧﺘﻘﺎﻻً ﻣﻦ ﻗﻮﻝ ﺇﻟﻰ ﻗﻮﻝ، ﻭﺟﺰﻣًﺎ ﺑﺎﻟﻘﻮﻝ ﻓﻲ ﻣﻮﺿﻊ، ﻭﺟﺰﻣًﺎ ﺑﻨﻘﻴﻀﻪ، ﻭﺗﻜﻔﻴﺮ ﻗﺎﺋﻠﻪ ﻓﻲ ﻣﻮﺿﻊ ﺁﺧﺮ، ﻭﻫﺬﺍ ﺩﻟﻴﻞ ﻋﺪﻡ ﺍﻟﻴﻘﻴﻦ،
ለዚህም ሲባል ሸይኹል ኢስላም እንዲህ ይላሉ:- "አንተ የፍልስፍና ባልተቤቶችን ከአንድ ንግግር ወደ አንድ ንግግር ባንድ ቦታ በንግግር መቁረጥን በሌላቦታ ደግሞ ያን ንግግራቸውን በማፍረስ እንዲሁም (ይባስ ብለው) የዚያን የንግግር ባልተቤት በሌላ ቦታ በማክፈር ታገኛቸዋለህ ይህ ደግሞ (በያዙት አቋም ላይ) እርግጠኝነት እንደሌላቸው መረጃ ነው" መጅሙኡል ፈታዋ 4/ 50
ሸይኽ ሙሀመድ ሰኢድ ረስላን እንዲህ ይላአሉ:- "ከቢዳአ ሰዎች አንዱ በአንድ መንገድ ላይ ያነጋል በሌላ መንገድ ላይ ያመሻል ከልቦና እና ከአስተያየት ጋር ከመገለበበጥ አይወገድም በአንድ ነገር ላይ አይፀናም ምክኒያቱም እሱ ዘንድ (የሚፀናበት) እርግጠኛ የሆነ ነገር የለም
አህሉሱናዎች ጋር (የሚፀኑበት) ቁራአን እና ሀዲስ አለ እነሱም መልእክተኛው ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም የመጡባቸው እውነታዎች ናቸው" [ምንጭ ደዓኢሙ ሚንሀጅ ኑቡዋ (65)]
ሁዘይፋ ረዲየላሁ አንሁ እንዲህ ይላል:-
"እውነተኛ ጥመት ብሎ ማለት መጥፎ የምትለውን ነገር ጥሩ አድርገህ ልትመለከት ነው ወይንም ጥሩ የምትለውን መጥፎ አድርገህ ልትመለከት ነው በዲን ላይ መገለባበጥን አደራህን የአላህ ዲን አንድ ነው" [አብረዛቅ ፊል ሙሰነፍ (11/249) አላለካእይ (120)]
"(ሰለፎች) በዲን ላይ መገለባበጥን ይጠሉ ነበር" [አል-ኢባነቱል ኩብራ(574)]
ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላአሉ:-
"መድሀኒት የለለው በሽታ በዲን ላይ መከረባበት ነው" [አልኢባነቱል ኩብራ (576)]
አሁንም በሀቅላይ ለመፅናት ከሚያግዙን ነገሮች ክርክርን እና በዲን ላይ ጭቅጭቅን መተው
ﻭﻟﻬﺬﺍ يقول – ﻋﻤﺮ ﺑﻦ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﻌﺰﻳﺰ:- ﻣﻦ ﺟﻌﻞ ﺩﻳﻨﻪ ﻏﺮﺿًﺎ ﻟﻠﺨﺼﻮﻣﺎﺕ ﺃﻛﺜﺮ ﺍﻟﺘﻨﻘﻞ
ለዚህም ሲል ኡመር ኢብኑ አብዱልአዚዝ እንዲህ ይላል "ዲኑን ክርክር ያደረገ መገለባበጥ ያበዛል" መጅሙኡል ፈታዋ
ሌላው ለሰባት ከሚረዳ ነገር ቂራአት መቅራት ቂራአት የቀራ ሰው እና ጃሂል መቸም ቢሆን ሊነፃፀር አይችልም በተለይ በዚህ ሹበሀ በበዛበት ዘመን ከምን በላይ ቂራአት አስፈላጊ ነው እውቀት ከሌለን ጯሂን ሁሉ እነከተላለን ሰዎች ሂዱ ሲሉን እነሄዳለን ተቀመጡ ሲሉንም እንቀመጣለን እንደው ባጭሩ ኢልም ከሌለን የጯሂ ሁሉ ተከታይ ነው የምንሆነው በቃ ድምፁን ከፍ አድርጎ የጮህ ሁሉ ሀቅ ላይ ያለ ነው የሚመስለን
በመቀጠል አላህ በሀቅ ላይ እንዲያፀናን ዘውትር ዱአ ማድረግ አለብን
ኡሙ ሰለማ እንዳስተላለፈችው የነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም ብዙዱአ "አንተ ልቦችን የምታገለባብጥ (ጌታ ሆይ) ልቤን በአንተ ሀይ ማኖት ላይ አፅናልኝ" ነበር ትላለች (ትርሚዝይ ዘግበውታል)
እኛም እነዚህን እና መሰል ዱአዎች ሰባት እንዲሰጠን ማብዛት አለብን
አላህ በመንሀጀ ሰለፍ ላይ ፀንተው መጨረሻቸው አምሮላቸው ከሚሞቱት ያድርገን
ወንድማችሁ ኢብኑ ሙሀመድዘይን (ሀምሌ 21/2008)