Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

“ደህና አባት እንዳላት ‘ገብሬ ይሙት!’” አለች gtm

“ደህና አባት እንዳላት ‘ገብሬ ይሙት!’” አለች
“ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው” ቢለኝ
ወረረኝ፣ ቀፈፈኝ አካሌን ነዘረኝ
እንኳን ፈጣሪዋን ሴት ወላጇን ላትወልድ
ሰው እንዲህ ይቀደድ
ወይ ጉድ!!!
“ስጋ ለብሶ ቅብጥርሶ” ብዙ ቢቀባጠር
ሀሰት እውነት ላይሆን ሺ ጊዜ ቢነገር
ግመል ሰርቆ ማጎንበሱ ላያዋጣ ነገር
ሰው ፈጣሪን ላይወልድ ማንም ቢጠረጥር
ሺ አመት ቢደሰኮር እልፍ አእላፍ ቢዘመር
በራስ ህሊና ላይ ካልታመፀ በቀር፡፡
የት አለ ሳይንሱ እንዴት ነው ብልሃቱ?
የሰው ልጅ ፈጣሪን የሚወልድበቱ?
“ማነው መልሱን የሚያውቅ?”
ብለን ብንጠይቅ
ወለቱ ተነስታ
“በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ
ተኮማትሮ ተጨማዶ….”
ማስረጃውስ?” ስንል ማንም አይነግረንም
ይህንንማ ወለቱ
ሰማነው ሰማነው ሰማነው ግን ምንም!!!
ወለቱ ቢጨንቃት አምጣ አምጣ
ማጣፊያው ቢቸግር ማስረጃ ብታጣ
መፅሀፉን ሳይሆን አባን አጣቀሰች
አየ የሷ ነገር
“ደህና አባት እንዳላት ‘ገብሬ ይሙት!’” አለች፡፡
https://www.facebook.com/IbnuMunewor