Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

እናቶች ሆይ ያለ ሸሪዐዊ ምክንያት ልጅን ጡት መከልከል ከባድ ወንጀል ነው!!

እናቶች ሆይ ያለ ሸሪዐዊ ምክንያት ልጅን ጡት መከልከል ከባድ ወንጀል ነው!!
ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የአንዳንድ ወንጀለኞችን ቅጣት አስመልክቶ በህልማቸው ስላዩት ሲያነሱ እንዲህ ይላሉ "ከዚያም (መልአኩ) ወሰደኝ። ጡታቸውን እባቦች የሚነድፏቸው ሴቶችን አየሁ።
‘ምንድን ነው የነዚህ ሁኔታ?’ አልኩኝ።
‘እነዚህ ጡታቸውን ከልጆቻቸው የሚከለክሉ ናቸው’ ተባለ።”
ሸይኹልአልባኒ ረሒመሁላህ ከዚህ ሐዲሥ ስር እንዲህ የሚል ሐሳብ አስፍረዋል። "በዚህ ውስጥ አንዳንድ ሚስቶች ጡታቸው እንዳይወድቅ በማሰብ በከሀዲዎች ወይም በጋጠ ወጦች በመመሳሰል ያለ ሸሪዐዊ ምክንያት ልጆቻቸውን አርቲፊሻል ጡት ማጥባታቸው ሐራም እንደሆነ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አለ።
(ሶሒሑልመዋሪድ: 1509)