Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

የሸዕባንን ወር ጾም

Ahmed Adem's photo.
አሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱሏህ
" የሸዕባንን ወር ጾም "
ሸዕባንን መጾም በተመለከተ ሁለት አይነት ሐዲሦች የተዘገቡ ሲሆን አንደኛው ቡኻሪይና ሙስሊም ከናታችን ዓኢሻ ረዲየሏሁ ዐንሃ ያስተላለፉት ሰሒሕ ሐዲሥ ነው (( ነቢዩ የሸዕባንን ወር ቀናቶችን አብዛኞቹን በጾም ያሳልፏቸው እንደነበረ ያሚያመላክት ሐዲሥ ሲሆን ))
ሁለተኛው ሐዲሥ ኢማም አትቲርሚዚይ፣ አቡ ዳውድና ሌሎችም የዘገቡት ሲሆን አብዛኞች የሐዲሥ ምሁራን ደዒፍ እንደሆነ ተናግረዋል ሀዲሡም እንዲህ ይላል (( የሸዕባን ወር ግማሽ ከሆነ በኋላ አትጹሙ))
ሁለቱንም ሐዲሦችን የሚያስታርቅውና በዚህ ነጥብ ላይ ትክክለኛ አቋም የሆነውም የሚከተለው ነው፥
" ሸዕባን ወር ከተጋመሰ (ከወሩ 15 ቀናት ካለፉ) በኋላ መጾም መጀመር ይጠላል
ከዛ በፊት የጀመረ ሰው ግን ሸዕባንን መጾም ይችላ::
አጿጿሙን በተመለከተ፥ ከፈለጉ አለፍ አለፍ እያሉ፣ ከፈለጉ ደግሞ አንድ ቀን እየጾሙ ሌላ ቀን እያረፉ፣ ከፈለጉም የተወሰኑ ቀናትን በመደዳ እየጾሙ ከዛም መሀል ላይ እያፈጠሩ ወዘተ ሁሉም ይቻላ::
ወሩን በሙሉ ምንም ሳያፈጥሩ መጾም ግን አይቻልም::
በቋሚነት የሚጾሙት የሱና ጾም ወይም የቀዷ ካልሆነ በስተቀር፥ የውም አሽሸክ ማለትም ረመዷን ዛሬ ነው ወይስ ነገ የሚባልበትን የጥርጣሬ ቀን መጾም አይቻልም::
ወሏሁ አዕለም
بلغنا الله وإياكم رمضان بأمن وإيمان
وغفر لنا ولوالدينا وللمؤمنين

Post a Comment

0 Comments