Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ኢስላምን ከጃሂሊያ ከለየህ ወሀብይ ይሉሃል!


ኢስላምን ከጃሂሊያ ከለየህ ወሀብይ ይሉሃል!
ከተላላቅ የአልጄሪያ ኡለማዎች መካከል እ.ኤ.አ 1960 ያለፉት ሸይኽ ጠይብ አል–ዑቅቢ "እንዲህ ቢሉኝ እንዲህ አልኳቸው" የሚል መጣጥፋቸው ይህንን ብለዋል፤ « ሰዎች ‘ያንተ እምነት የወሀብዮች አይነት ነው’ ሲሉኝ፤ "ይህ ከሆነማ ወሀብዮች ማለት የአላህን አንድነት የሚያረጋግጡ (ሙወሂዶች) ናቸው ማለት ነው" በማለት እመልስ ነበር» ሲሉ ፅፈዋል።»
ምንጭ፦ ሺሀብ ጋዜጣ ኦክቶበር 27/1927
በሌላም ፅሁፋቸውም፤
«በዳእዋ ስራ ህዝባችንን ግንዛቤ ማስጨበጥና በትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ ማነፅ እንፈልጋለን። ይህንንም በሁለት ነጥቦች ማስቀመጥ ይቻላል።
1) ከአላህ በስተቀር ማንንም አለማምለክ፤
2) አላህን የምናመልከው እርሱ በደነገገውና ከሱ ዘንድ በመጣው መመሪያ መሆን አለበት
ወሀብያ ማለት፤ አላህ ለባሮቹ በደነገገው መልኩ እርሱን በብቸኝነት ማምለክ ከሆነ፤ ይህ አላህን የምናመልክበት ዲናችን፣ መዝሃባችን ነው። ገር የሆነው መንገዳችን እሱ ነው። በዚህ ላይ ኖረን በዚሁ አቋም ላይ እንሞታለን።
በአላህ ፍቃድም ከሚድኑት ሆነን እንቀሰቀሳለን።»
ምንጭ፦ ሱና ጋዜጣ አፕሪል 22 1933 እትም ካቀረበው ፅሁፋቸው
እውነት ነው! ባሁኑ ጊዜ አላህን በብቸኝነት አምልኩ፤ ባእድ አምልኮ፣ ቀብር ማምለክ፣ ቅዱሳንን መጣራት አይገባም ያለ ሁሉ ወሀብይ ይባላል። በተለይም ባሁኑ ዘመን የጃሂሊያን ሽርክ ለማንገስ የሚሯሯጡት አህባሾች የጧት ማታ መዝሙር ሆኗል። ለመሆኑ ከሸይኽ ሙሀመድ አብዱልወሀብ ዳእዋ በፊትም ይሁን በኃላ፤ አራሱን ከተፅእኖ አላቆ ላስተዋለ፤ ይህ የሽርክ ተግባር ከኢስላማዊ አስተምህሮ ጋር ፍፁም የሚጋጭ የጃሂሊያ ቅሪት መሆኑን ያጣዋልን?
ኢስላም ማለትስ የአላህን አንድነት መባረጋገጥ ለርሱ ትእዛዛት ማደር መሆኑ ያጠራጥራልን?
አላህ ሆይ ከኛ መካከል የጃሂሊያ የሽርክ ጥሪ የተሸነገሉን ሁሉ የተውሂድን ብርሀን አሳያቸው! ወደ ተፈጥሯዊ ምልከታቸው መልሳቸው። አሚን!
መሰል መልእክቶችን ለማግኘት ፔጃችንን ላይክ ያድርጉ
ኢስላሚያ ላ ወሀቢያ
www.fb.com/wehabiya
قال الشيخ الطيب العقبي - رحمه الله - في مقال له بعنوان ( يقولون وأقول ) نشر في ( العدد 119 ) من جريدة " الشهاب " ( 30 ربيع الثاني 1346 هـ / 27 أكتوبر 1927 م ، ص 14 ) : ( يقولون لي : إن عقائدك هذه هي عقائد الوهابية ، فقلت لهم : إذن الوهابية هم الموحدون ) .
وقال - رحمه الله - في ( العدد 2 ) من جريدة " السنة " ( 22 ذي الحجة 1351 هـ / 17 أبريل 1933 م ، ص 7 ) : ( هذا وإن دعوتنا الإصلاحية - قبل كل شيء وبعده - هي دعوة دينية محضة ، لا دخل لها في السياسة ألبتة ، نريد منها تثقيف أمتنا وتهذيب مجتمعنا بتعاليم دين الإسلام الصحيحة ، وهي تتلخص في كلمتين : أن لا نعبد إلا الله وحده ، وأن لا تكون عبادتنا له إلا بما شرعه وجاء من عنده ...
وإذا كانت الوهابية : هي عبادة الله وحده بما شرعه لعباده ، فإنها هي مذهبنا وديننا وملتنا السمحة التي ندين الله بها وعليها نحي وعليها نموت ونبعث إن شاء الله من الآمنين ) .
أخوكم في الله صالح أحمد