Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ትዳርህን ተንከባከበው

‎~`~ትዳርህን ተንከባከበው~`~

 የአጋርህን ስሜት ተረድተህ
      ሃላፊነትህን ተወጣ
°°󾀽°°°°° ✅ °°°°°󾀽°°

የተንቢሃት ልዩ ሳምንታዊ መልዕክት ቁ• 11

① ስሜትን መረዳት

   ትዳር በህይወታችን ውስጥ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት ሲሆን የግለሰብ፣ የቤተሰብና የማህበረሰብ ኣልፎም ያጠቃላይ የሰው ልጆች መገንቢያ ማዕከል ነው። 

   በትዳር ዓለም በሌሎች የህይወት ዘርፎች የማይገኙ ክቡር ትሩፋቶች ይገኙበታል።

√ እውነተኛ አፍቃሪ
√ ሚስጥረኛ ወዳጅ
√ ከማንም የቀረበ ነውርን ሸፋኝ
√ የተባረከ ተተኪ ትውልድ
√ ቤተሰብ፣ አዳዲስ ዘመዶች…
√ ሀላል የሆነ እርካታ
√ የኔ ሚባል ደጋፊ  እና የመሳሰሉት

   ይህ እጅግ በጣም ብዙ ጥቅሞች ያሉበት ትዳር የሚባለውን ፕሮጀክት በአግባቡ ለመምራትና የሚጠበቀውን ጥቅም ለማግኘት ወሳኝ ከሚባሉት ነጥቦች ኣንዱ የትዳር ጓዶቹ መግባባት ነው።

   መግባባት ደግሞ የሚወለደው ኣንዱ ያንዱን ስሜትና ፍላጐት ሲገነዘብና አስፈላጊውን ምላሽ ሲሰጥ ነው።

   ለዚህም ማስተዋያ እንዲሆነን የአርዓያችንን የህይወት ታሪክ ስናስተውል ከምእመናን እናት ዓኢሻ ቢንቱ ሲዲቅ ረዲየላሁ ዐንሁም ጋር ሳሉ የገጠማቸውን ሲነግሩን እንዲህ ይላሉ።
     
   ሙስሊም በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ በሆነ ጉዳይ ቅር ሲላት ወይም ደስተኛ ስትሆን ያውቁባት ነበር።

   በዚህም ጥናታቸው ባለቤታቸው በመሃላዋ ውስጥ እንኳን  ቅሬታዋን የምትገልፅበትን መንገድ በተከታዩ መልክ ገልፀዋል።

« በኔ ላይ ደስተኛ ስትሆኚም ሆነ በኔ ላይ ስትቆጪ አውቃለሁኝ።

   በኔ ላይ ደስተኛ በሆንሽ ግዜ 
በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ።

   በኔ ላይ በተቆጣሽ ግዜ ደግሞ:
በኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ ። »

   ቁጣዋንና ደስታዋን ለይተው እንደሚያውቁት እየገለፁ ነው።

   አስተውሉ!

   ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ክፉ ቃል አልወጣትም፣ ጮሃም ተንጫጭታም በቁጣ አልተናገረችም። ነገር ግን በሳቸው ላይ ቅር ስተሰኝ አጋጣሚ መሃላ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲገጥማት በስማቸው መማልን ታኮርፍና በነቢዩ ኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ ትላለች።

   ቁጣዋ ሲለቃት ግን በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ ስትል ትምላለች።

   ይህንንም ባህሪዋን መልእክተኛው አወቁባትና ነገሯትም።

   ስለዚህም የትዳር አጋሮቻችንን ስሜት እዚህ ድረስ ለይቶ ለማወቅ የቅርብ ክትትል ማድረግህ እቤትህ ያለውን ችግር ለመረዳት ራስህንም፣ እሷንም ለማረም ይረዳሃል።

   የአላህ መልእክተኛ ﷺ ውዷ ባለቤታቸው ዓኢሻ ቢንት አቢ በክርም ሆነች ሌሎች የምእመናን እናቶች (ረዲየላሁ ዐንሁነ አጅመዒን) በሆነ ጉዳይ ቅር መሰኘታቸውንና ኣለመሰኘታቸውን በትኩረት ይከታተላሉ ይረዱታልም።

   እኛም አርዓያነታቸውን አምነን እስከተቀበልንና በተግባር ማዋሉም ተገቢ እንደሆነ እስካመንበት ድረስ፤ ለትዳራችን ስኬት ግራ ቀኝ ብለን ሌላ መፍትሄ ከምናፈላልግ ወይም እያቋቋምን ከምናፈርስ ወደ መመርያችን እንመለስ።

ትዳር ሲባል :

~ ቤት መመስረት፣
~ ገብቶ መብላት፣
~ ለብሶ መውጣት፣
~ ደርሶ መተኛትና
ልጅን መውለድ ብቻ አይደለም።

   የራሱ የሆነ ለየት ያለ ዓለም ከመሆኑ አንፃር ጣዕሙና ለዛውም እንደየ ባለትዳሮቹ ይፈራረቃል።

በተሰማራህበት መስክ 

•> ህዝብን የምትቀርፅ ሸይኽ ብትሆን፣ 
•> ቀን ከሌት የምትገስፅ ዳዒ ብትሆን፣ 
•> ከሆነ አመራር ድርሻ ቢኖርህ፣
•> ታታሪ ነጋዴም ብትሆን፣
•> ባለ ዓላማ ተማሪ ብትሆን፣
•> ተመራማሪም አጥኚ ብትሆን፣
•> ኑሮን ምትታገል ቅጥረኛም ብትሆን… …

    እቤትህ የተገነባው በነበልባል ከሆነ በተለያዩ ክስተቶች እርር… ድብን… ቅጥል የምትልበት እድሉ ስለሚሰፋ ሌሎች ዓላማዬ ብለህ የተነሳህለትን ጉዳዮችህን በተግባር ማዋል የማትችል ትሆናለህ።

    ለብሰህ ሲያዩህ የተመቸህ ምሰል እንጂ አቅልህ በሆነ ነገር ርቆሃል።

   እንደው ፈገግ ስትልና እኩል ስታወራ የተደላደልክ ብትመስልም ዘወር ስትል የምትተነፍሰው እሳት ነው።

   በቆምክበት መድረክ ሁሉ የተረበሽክ ስለምትሆን ብዙ ነገርህ ይምታታል።

   የዛሬው ስራህን መገምገሚያ፣ ለነገው ፕሮግራምህ መዘጋጃ የሚሆን ሰላማዊ ቤት ስለሌለህ የቆምክለት ጉዳይም ቤትህም ስልችት ይሉሃል።

   የራስህንም ሆነ የባለቤትህን ማንነት በጥልቅ ስላልተረዳህ ጥፋትህን መደበቂያ ሰበብ ፈላጊ ትሆናለህ።

   ሁሌም ተሰቃየሁ እንጂ አሰቃይቼ ይሆን ብለህ ራስህን አትገመግምም።

   በዚህም ሰበብ ወደቤትህ በመጣህ ቁጥር እሷን ማሸነፍያ ቃላቶችን ስታሰላስል አእምሮህን ወጥረህ…… መሆን የሚገባህንና መስራት የነበረብህን በርካታ ነገሮች ትዘላቸዋለህ።
  
   ሰላም የሌለው ትዳር ማለት የበሽታዎች ሁሉ በሽታ ነው። ያውም ታማሚውና አስታማሚው እኩል የተያዙበት በሽታ።

   የዚህ ሁሉ አብዛኛው ሰበቡ አንተው ትሆናለህ።

   ሰበብ አታፈላልግ ስህተቷን ብቻ አታጉላ! በደልንም ፍራ!

       °°°°󾀽°°°✅°°°󾀽°°°

   ጥቂት የማይባሉ እንስቶች ብዙውን ግዜ በንጭንጬ፣ በጩኸት፣ በችኮላና፣ በቁጣ ሃሳባቸውን ይገልፁ ይሆናል።

  ብሶታቸውንም በስድብ፣ በእርግማን፣ በወቀሳና በለቅሶ ያሳዩም ይሆናል። 

   የዚህን ግዜ ከውጭ ለሚመለከት ታዛቢ ሁለት ነገሮችን ያንፀባርቅለታል።

~ ወይ በጣም የተበደለች
~ ወይ ደግሞ አስቸጋሪ ሚስት ነች የሚል ጥርጣሬ ላይ ያደርሰዋል።

   እውነታው ግን አንተጋ ግልፅ ነው። ተበዳይነቷም ሆነ አስቸጋሪነቷ እዚህ ደረጃ ሳይደርስ ማከም የምትችልበት ስልጣንና መፍትሄዎች ሁሉ ተሰጥተውሃል።

    ከዚያ ያለፈ ነገር ሆኖ መለያየት ቢከሰት እንኳ ቀድመህ የሚጠበቅብህን ከተወጣህ የሚቆጭህ አትሆንም።

  ለሷም የእድሏን ላንተም የድርሻህን የሚሰጥ አምላክ እኮ ነው ያለን። የምን በራስም በሰውም ህይወት መቀለድ ነው❗

 قال تعالى: (وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللّهُ كُلاًّ مِّن سَعَتِهِ وَكَانَ اللّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا) النساء 130 

« ቢለያዩም አላህ ሁሉንም በችሮታው ያብቃቃቸዋል። አላህም ችሮታው ሰፊ ጥበበኛ ነው። » አል ኒሳእ 130

  ሁሉም ነገር አስተዳደርና መሪ እንዳለው ሁሉ ትዳርም ብቁ መሪና የሰከነ አስተዳዳሪ ይፈልጋል።

   በጣም ጥቃቅን ፍሞችን ከባሎች የአያያዝና የማብረድ ጉድለት የተነሳ በእንስቶቹ እጅ ሲነድ ታየዋለህ።

   ወንዶች ዘንድ ተወቃሿ ፣ ተተቺዋና ድሮም እናንተ እየተባለ የሚተረተው በሚስቶች ሲሆንም ትሰማለህ።

   በዚያው ልክ ሴቶች ዘንድም ጠቅለል ተደርጎ " ወንዶች ስትባሉ እንደው… … " እየተባለ ሲወገዝ ትሰማለህ። 

   ይኸ ጥቅል ወቀሳ ግን አጥፊዎችን ከመሸሸግ ውጪ ምንም ጥቅም የለውም። 

   ይልቅ ከምርጫ ጀምሮ ራስህን አበጅተህና አውቀህ ከገባህበት፤ ከዚያም የሚነሱ አለመግባባቶችን በትእግስት መፍታት ከቻልክ ቤትህ የዱንያ ጀነት አርፎበታልና ምቾታችሁ፣ ድሎታችሁና ደስታችሁ ሁሌም የሚረሳ አይሆንም።

   እርግጥ ነው አንተም ሰው ነህና ድክመትም ስህተትም አይለይህም። እንዴት ቤትህን በስርኣት ማስተዳደር ያቅተሃልም አይባልም።

    ነገር ግን ሃላፊነትህን ለመወጣት ንቁ ተሳትፎ ካደረክ በአላህ ፈቃድ ብዙዎቹን የትዳርህን ቁስሎች ማከም ትችላለህ።

   ለዚህ ብቃትህ ወሳኙ ቁልፍ ደግሞ የአጋርህን ግንዛቤ፣ ባህሪ፣ ፍላጎትና ስሜት እንዲሁም አቅም ማወቅ ነው። ከዚያም ተመጣጣኝ ምላሽ መስጠትህ ነው።

   የዚያን ግዜ ድክመታችሁ ማሳበቢያ ስለማይኖረው የግድ ራሳችሁን ለማረም ደፋቀና ትላላችሁ።

   ያለዚያ እያለቀስክ ወይም እያስለቀስክ በሁለት በደሎች መሃል መኖር ሊከሰትብህ ይችላል። 

   መከላከል እየቻሉ ራስን ለጉዳት መዳረግም ሆነ፤ ሌሎችን የሚጎዳ ነገር ማድረግ ደግሞ በነቢያችን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንደበት የተኮነነ ጉዳይ ነው።

قال النبي صلى الله عليه وسلم : (لَا ضَرَرَ وَلَا ضِرَارَ) أخرجه أحمد (2865) وابن ماجه (2341) وصححه الألباني في صحيح ابن ماجه 

«(በሸሪዓ) ጉዳትም መጎዳዳትም የለም! » አልሀዲስ 
 
قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( اتقوا الظلم، فإن الظلم ظلمات يوم القيامة ) رواه مسلم 

«በደልን ተጠንቀቁ! የትንሳዔው እለት በደል ጨለማዎች ናትና» ሙስሊም ዘግበውታል

አንተም አትበድል! እንዲበድሉህም አትመቻች!

አላህ የተሳካላቸው ባለ ትዳሮች ያድርገን!!

በደል ከማድረስም ፣ ተበዳይ ከመሆንም ይጠብቀን!!

አሚን!!

#መጠይቅ
   የትዳር ውስጥ ችግሮችን መፍታት በተመለከተ ከባልም ይሁን ከሚስት ምን ምን አስተዋፅኦ ይጠበቃል  ❓❓

والله أعلم، وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليما كثيرا.

ፔጃችንን ያስተዋውቁ
www.facebook.com/tenbihat

------------------
󾔧abufewzan 23/4/1436
13 Feb 2015‎
~`~ትዳርህን ተንከባከበው~`~
የአጋርህን ስሜት ተረድተህ
ሃላፊነትህን ተወጣ
°°°°°°° ✅ °°°°°°°
የተንቢሃት ልዩ ሳምንታዊ መልዕክት ቁ• 11
① ስሜትን መረዳት
ትዳር በህይወታችን ውስጥ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት ሲሆን የግለሰብ፣ የቤተሰብና የማህበረሰብ ኣልፎም ያጠቃላይ የሰው ልጆች መገንቢያ ማዕከል ነው።
በትዳር ዓለም በሌሎች የህይወት ዘርፎች የማይገኙ ክቡር ትሩፋቶች ይገኙበታል።
√ እውነተኛ አፍቃሪ
√ ሚስጥረኛ ወዳጅ
√ ከማንም የቀረበ ነውርን ሸፋኝ
√ የተባረከ ተተኪ ትውልድ
√ ቤተሰብ፣ አዳዲስ ዘመዶች…
√ ሀላል የሆነ እርካታ
√ የኔ ሚባል ደጋፊ እና የመሳሰሉት
ይህ እጅግ በጣም ብዙ ጥቅሞች ያሉበት ትዳር የሚባለውን ፕሮጀክት በአግባቡ ለመምራትና የሚጠበቀውን ጥቅም ለማግኘት ወሳኝ ከሚባሉት ነጥቦች ኣንዱ የትዳር ጓዶቹ መግባባት ነው።
መግባባት ደግሞ የሚወለደው ኣንዱ ያንዱን ስሜትና ፍላጐት ሲገነዘብና አስፈላጊውን ምላሽ ሲሰጥ ነው።
ለዚህም ማስተዋያ እንዲሆነን የአርዓያችንን የህይወት ታሪክ ስናስተውል ከምእመናን እናት ዓኢሻ ቢንቱ ሲዲቅ ረዲየላሁ ዐንሁም ጋር ሳሉ የገጠማቸውን ሲነግሩን እንዲህ ይላሉ።
ሙስሊም በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ በሆነ ጉዳይ ቅር ሲላት ወይም ደስተኛ ስትሆን ያውቁባት ነበር።
በዚህም ጥናታቸው ባለቤታቸው በመሃላዋ ውስጥ እንኳን ቅሬታዋን የምትገልፅበትን መንገድ በተከታዩ መልክ ገልፀዋል።
« በኔ ላይ ደስተኛ ስትሆኚም ሆነ በኔ ላይ ስትቆጪ አውቃለሁኝ።
በኔ ላይ ደስተኛ በሆንሽ ግዜ
በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ።
በኔ ላይ በተቆጣሽ ግዜ ደግሞ:
በኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ ። »
ቁጣዋንና ደስታዋን ለይተው እንደሚያውቁት እየገለፁ ነው።
አስተውሉ!
ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ክፉ ቃል አልወጣትም፣ ጮሃም ተንጫጭታም በቁጣ አልተናገረችም። ነገር ግን በሳቸው ላይ ቅር ስተሰኝ አጋጣሚ መሃላ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲገጥማት በስማቸው መማልን ታኮርፍና በነቢዩ ኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ ትላለች።
ቁጣዋ ሲለቃት ግን በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ ስትል ትምላለች።
ይህንንም ባህሪዋን መልእክተኛው አወቁባትና ነገሯትም።
ስለዚህም የትዳር አጋሮቻችንን ስሜት እዚህ ድረስ ለይቶ ለማወቅ የቅርብ ክትትል ማድረግህ እቤትህ ያለውን ችግር ለመረዳት ራስህንም፣ እሷንም ለማረም ይረዳሃል።
የአላህ መልእክተኛ ﷺ ውዷ ባለቤታቸው ዓኢሻ ቢንት አቢ በክርም ሆነች ሌሎች የምእመናን እናቶች (ረዲየላሁ ዐንሁነ አጅመዒን) በሆነ ጉዳይ ቅር መሰኘታቸውንና ኣለመሰኘታቸውን በትኩረት ይከታተላሉ ይረዱታልም።
እኛም አርዓያነታቸውን አምነን እስከተቀበልንና በተግባር ማዋሉም ተገቢ እንደሆነ እስካመንበት ድረስ፤ ለትዳራችን ስኬት ግራ ቀኝ ብለን ሌላ መፍትሄ ከምናፈላልግ ወይም እያቋቋምን ከምናፈርስ ወደ መመርያችን እንመለስ።
ትዳር ሲባል :
~ ቤት መመስረት፣
~ ገብቶ መብላት፣
~ ለብሶ መውጣት፣
~ ደርሶ መተኛትና
ልጅን መውለድ ብቻ አይደለም።
የራሱ የሆነ ለየት ያለ ዓለም ከመሆኑ አንፃር ጣዕሙና ለዛውም እንደየ ባለትዳሮቹ ይፈራረቃል።
በተሰማራህበት መስክ
•> ህዝብን የምትቀርፅ ሸይኽ ብትሆን፣
•> ቀን ከሌት የምትገስፅ ዳዒ ብትሆን፣
•> ከሆነ አመራር ድርሻ ቢኖርህ፣
•> ታታሪ ነጋዴም ብትሆን፣
•> ባለ ዓላማ ተማሪ ብትሆን፣
•> ተመራማሪም አጥኚ ብትሆን፣
•> ኑሮን ምትታገል ቅጥረኛም ብትሆን… …
እቤትህ የተገነባው በነበልባል ከሆነ በተለያዩ ክስተቶች እርር… ድብን… ቅጥል የምትልበት እድሉ ስለሚሰፋ ሌሎች ዓላማዬ ብለህ የተነሳህለትን ጉዳዮችህን በተግባር ማዋል የማትችል ትሆናለህ።
ለብሰህ ሲያዩህ የተመቸህ ምሰል እንጂ አቅልህ በሆነ ነገር ርቆሃል።
እንደው ፈገግ ስትልና እኩል ስታወራ የተደላደልክ ብትመስልም ዘወር ስትል የምትተነፍሰው እሳት ነው።
በቆምክበት መድረክ ሁሉ የተረበሽክ ስለምትሆን ብዙ ነገርህ ይምታታል።
የዛሬው ስራህን መገምገሚያ፣ ለነገው ፕሮግራምህ መዘጋጃ የሚሆን ሰላማዊ ቤት ስለሌለህ የቆምክለት ጉዳይም ቤትህም ስልችት ይሉሃል።
የራስህንም ሆነ የባለቤትህን ማንነት በጥልቅ ስላልተረዳህ ጥፋትህን መደበቂያ ሰበብ ፈላጊ ትሆናለህ።
ሁሌም ተሰቃየሁ እንጂ አሰቃይቼ ይሆን ብለህ ራስህን አትገመግምም።
በዚህም ሰበብ ወደቤትህ በመጣህ ቁጥር እሷን ማሸነፍያ ቃላቶችን ስታሰላስል አእምሮህን ወጥረህ…… መሆን የሚገባህንና መስራት የነበረብህን በርካታ ነገሮች ትዘላቸዋለህ።
ሰላም የሌለው ትዳር ማለት የበሽታዎች ሁሉ በሽታ ነው። ያውም ታማሚውና አስታማሚው እኩል የተያዙበት በሽታ።
የዚህ ሁሉ አብዛኛው ሰበቡ አንተው ትሆናለህ።
ሰበብ አታፈላልግ ስህተቷን ብቻ አታጉላ! በደልንም ፍራ!
°°°°°°°✅°°°°°°
ጥቂት የማይባሉ እንስቶች ብዙውን ግዜ በንጭንጬ፣ በጩኸት፣ በችኮላና፣ በቁጣ ሃሳባቸውን ይገልፁ ይሆናል።
ብሶታቸውንም በስድብ፣ በእርግማን፣ በወቀሳና በለቅሶ ያሳዩም ይሆናል።
የዚህን ግዜ ከውጭ ለሚመለከት ታዛቢ ሁለት ነገሮችን ያንፀባርቅለታል።
~ ወይ በጣም የተበደለች
~ ወይ ደግሞ አስቸጋሪ ሚስት ነች የሚል ጥርጣሬ ላይ ያደርሰዋል።
እውነታው ግን አንተጋ ግልፅ ነው። ተበዳይነቷም ሆነ አስቸጋሪነቷ እዚህ ደረጃ ሳይደርስ ማከም የምትችልበት ስልጣንና መፍትሄዎች ሁሉ ተሰጥተውሃል።
ከዚያ ያለፈ ነገር ሆኖ መለያየት ቢከሰት እንኳ ቀድመህ የሚጠበቅብህን ከተወጣህ የሚቆጭህ አትሆንም።
ለሷም የእድሏን ላንተም የድርሻህን የሚሰጥ አምላክ እኮ ነው ያለን። የምን በራስም በሰውም ህይወት መቀለድ ነው
قال تعالى: (وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللّهُ كُلاًّ مِّن سَعَتِهِ وَكَانَ اللّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا) النساء 130
« ቢለያዩም አላህ ሁሉንም በችሮታው ያብቃቃቸዋል። አላህም ችሮታው ሰፊ ጥበበኛ ነው። » አል ኒሳእ 130
ሁሉም ነገር አስተዳደርና መሪ እንዳለው ሁሉ ትዳርም ብቁ መሪና የሰከነ አስተዳዳሪ ይፈልጋል።
በጣም ጥቃቅን ፍሞችን ከባሎች የአያያዝና የማብረድ ጉድለት የተነሳ በእንስቶቹ እጅ ሲነድ ታየዋለህ።
ወንዶች ዘንድ ተወቃሿ ፣ ተተቺዋና ድሮም እናንተ እየተባለ የሚተረተው በሚስቶች ሲሆንም ትሰማለህ።
በዚያው ልክ ሴቶች ዘንድም ጠቅለል ተደርጎ " ወንዶች ስትባሉ እንደው… … " እየተባለ ሲወገዝ ትሰማለህ።
ይኸ ጥቅል ወቀሳ ግን አጥፊዎችን ከመሸሸግ ውጪ ምንም ጥቅም የለውም።
ይልቅ ከምርጫ ጀምሮ ራስህን አበጅተህና አውቀህ ከገባህበት፤ ከዚያም የሚነሱ አለመግባባቶችን በትእግስት መፍታት ከቻልክ ቤትህ የዱንያ ጀነት አርፎበታልና ምቾታችሁ፣ ድሎታችሁና ደስታችሁ ሁሌም የሚረሳ አይሆንም።
እርግጥ ነው አንተም ሰው ነህና ድክመትም ስህተትም አይለይህም። እንዴት ቤትህን በስርኣት ማስተዳደር ያቅተሃልም አይባልም።
ነገር ግን ሃላፊነትህን ለመወጣት ንቁ ተሳትፎ ካደረክ በአላህ ፈቃድ ብዙዎቹን የትዳርህን ቁስሎች ማከም ትችላለህ።
ለዚህ ብቃትህ ወሳኙ ቁልፍ ደግሞ የአጋርህን ግንዛቤ፣ ባህሪ፣ ፍላጎትና ስሜት እንዲሁም አቅም ማወቅ ነው። ከዚያም ተመጣጣኝ ምላሽ መስጠትህ ነው።
የዚያን ግዜ ድክመታችሁ ማሳበቢያ ስለማይኖረው የግድ ራሳችሁን ለማረም ደፋቀና ትላላችሁ።
ያለዚያ እያለቀስክ ወይም እያስለቀስክ በሁለት በደሎች መሃል መኖር ሊከሰትብህ ይችላል።
መከላከል እየቻሉ ራስን ለጉዳት መዳረግም ሆነ፤ ሌሎችን የሚጎዳ ነገር ማድረግ ደግሞ በነቢያችን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንደበት የተኮነነ ጉዳይ ነው።
قال النبي صلى الله عليه وسلم : (لَا ضَرَرَ وَلَا ضِرَارَ) أخرجه أحمد (2865) وابن ماجه (2341) وصححه الألباني في صحيح ابن ماجه
«(በሸሪዓ) ጉዳትም መጎዳዳትም የለም! » አልሀዲስ
قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( اتقوا الظلم، فإن الظلم ظلمات يوم القيامة ) رواه مسلم
«በደልን ተጠንቀቁ! የትንሳዔው እለት በደል ጨለማዎች ናትና» ሙስሊም ዘግበውታል
አንተም አትበድል! እንዲበድሉህም አትመቻች!
አላህ የተሳካላቸው ባለ ትዳሮች ያድርገን!!
በደል ከማድረስም ፣ ተበዳይ ከመሆንም ይጠብቀን!!
አሚን!!
‪#‎መጠይቅ‬
የትዳር ውስጥ ችግሮችን መፍታት በተመለከተ ከባልም ይሁን ከሚስት ምን ምን አስተዋፅኦ ይጠበቃል
والله أعلم، وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليما كثيرا.
ፔጃችንን ያስተዋውቁ
www.facebook.com/tenbihat
------------------
abufewzan 23/4/1436
13 Feb 2015