Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

የ18 አደባባዩ ቆሪጥ


بسم الله الرحمن الرحيم الحمد لله رب العالمين، وصلى الله وسلم على رسوله  
18 አደባባዩ ቆሪጥ አቂዳ ከምንም ነገር በላይ ቅድሚያ ይሰጠው፡፡ አላህ እንዲጀመር ያዘዘበት፤ 124 ሺህ ነብያቱ ይህንን አቂዳ የመጀመሪያ አርስታቸው አድርገው የተነሱበት፤ጀነት እና ጀሃነም የተዘጋጁለት፤ መለኮታዊ መፀሃፍት ሁላ የተላኩበት አላማ ነው፤አቂዳ፡፡ ወደ አርስቱ ስንመለስ ከጦር ሃይሎች እስከ ዊንጌት ባለው ቀለበት መንገድ ላይ የመኪና  አደጋ ይበዛል፡፡ በተለይ 18 አደባባይ የሚባለው ላይ፡፡ እውነታው የሚያሳየው ከዊንጌትወደ ጦር ሃይሎች ያለው መንገድ ቁልቁለት ስለሆነ አደጋ ይደርሳል፡፡የሚያሳዝነው ግን ሰዎች ያውም ሙስሊሞች ሰላት የሚሰግዱ ይህ አደጋ ሲደጋገም ‹‹18 አደባባይ ቆሪጥ ነው መኪናዎቹን የሚገለብጣቸው›› ይላሉ፡፡ ካስታወስን ቆሪጥ  በመባል የሚታወቀው ደብረዘይት ወንዝ ላይ የሚመለክ ጂን ነው፡፡ እንዲህ አይነት ክስተቶችን ሰዎች ጂን ነው የሚያደርጋቸው ብለው ካመኑ፤ ከዛ በኋላ ያለውን መገመት  ቀላል ነው፡፡ እሱም ‹‹በአመቱ ይታረድለት›› የሚባል ሽርካቸውን መዘዝ ያደርጉታል፡፡  ይህንን ነገር በአጭሩ እንቅጨው፡፡ 18 አደባባይ ወጣቶች ሰዉን እዚህ አርእስት ላይ  አንቁት፡፡ አላህ ለሁላችንም ኢኽላስ ይስጠን፡፡ ከጊዜ በኋላ ሊታረድለት ይችላል ያልኩት የሚከተለውን ኢትዬጵያውስጥ የሚሰራ ተመሳሳይ የሽርክ ተግባር ተምሳሌት አድርጌ ነው ፡፡ ግንበሃ የሚባል ቦታ (ከኮሶ በር ወደ ቻግኒ ሲኬድ ቅዳማጃ ሳይደረስአንድ ተራራማ እና አስቸጋሪ የሆነ መንገድ አለ፡፡ መኪኖች እየተገለበጡ ሲያስቸግሩ፤ የአካባቢው ሰዎች ጂኑ ነው ይህን የሚያደርገው በማለት በአመት ያርዱለታል፡፡ አንዳንዴ ድምፁን ሲጮህ  ሰማነው ሁሉ ይላሉ፡፡ በጣም የሚገርመው በመሰረቱአላህ የሰው ልጅ ከጂን በላይ  አልቆት ነበር፡፡ ከጂንም መልክተኛ ተልኮ አያውቅም፡፡ ከሰው ልጆች ወንድ ቢሆን እንጂ ፡፡ ድሮ ድሮ የሰው ልጅ ወደሆነ ዋሻ ሲገባ ጂኖች ፈርተው ይወጡ ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ  የሰው ልጅ ሽርክ ሲሰራ ክብሩን አጣና ጂንን መፍራትጀመረ፡፡                አላህን የፈራ ሁሉ   ይፈራዋል፤ አላህን ያልፈራ ሁሉንም ይፈራል፡፡