ማንቂያ ደውል! እስከመቼ ዲንን መቃረን?
የነብዩን (ﷺ) ቃል ከነፍሶት፣ ከጓደኞቾት እና ከማንም በላይ ያስበልጣሉ ወይንስ አያስበልጡም?
ነብዩ (ﷺ) “ለቀልድም ብሎ መዋሸት አይቻልም” ይሉናል፡፡
ዛሬ ዛሬ ፈረንጅ የሰራውን ሁሉ መስራት የሚፈልግ አለ፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ሰውን ለማስደንገጥ፣ ያልሞተውን ሞተ፣ ያልተገጨውን ተገጨ፣ ያልደረሰውን ደረሰ ብሎ ሰዎችን ማስደንገጥ የኢስላም አካል አይደለም፡፡ ኢስላም አይደለም ለማስደንገጥ ለቀልድ መዋሸትን ከልክሏል፡፡ እባካችሁ እጅ እንስጥ ሙሉ ለሙሉ ከእዚህ እርኩስ ኩረጃ እንራቅ፡፡ ኢስላም ሙሉ ነው፡፡ ከፈረንጅ መኮረጅ አይፈልግም፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡