┄┄┉┉✽̶»̶̥
ቁርአን የአላህ ንግግር ሲሆን ቃሉም ትርጉሙም ከአላህ የመነጨና ጂብሪል ከአላህ በመስማት ወደ ነቢዩ ﷺ ያስተላለፈው ከብረዛና ከመዛባት የተጠበቀ መፅሐፍ ነው::
በአላህ መፃህፍት ማመን ከኢማን ማፅዘናት አንዱ ነው፡፡ ይሁንና ቁርአን ሌሎችን መፃህፍት የሚሰርዝ የሁሉም የበላይ ፈራጅና ነቢዩ ﷺ ከተላኩ በኃላ የሁሉም ሰውና ጋኔን መመሪያ በመሆኑ ከአላህ ዘንድ በወረዱና ከመበረዛቸው በፊት ባሉበት ሁኔታ በሁሉም መፃህፍት ማመን እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ቁርአንን ከሌሎች የምንለይባቸው እምነቶች አሉ ከነዚህ መለያዎቹ መካከል ፦
} ﺗَﺒَﺎﺭَﻙَ ﺍﻟَّﺬِﻱ ﻧَﺰَّﻝَ ﺍﻟْﻔُﺮْﻗَﺎﻥَ ﻋَﻠَﻰ ﻋَﺒْﺪِﻩِ ﻟِﻴَﻜُﻮﻥَ ﻟِﻠْﻌَﺎﻟَﻤِﻴﻦَ ﻧَﺬِﻳﺮًﺍ { ( ﺍﻟﻔﺮﻗﺎﻥ : 1 )
‹‹ያ ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስጠንቃቂ ይኾን ዘንድ ያወረደው (አምላክ) ክብርና ጥራት ተገባው፡፡›› (ፉርቃን 1)
በሌላም የቁርኣን አያት ለነብያችን ﷺ እንዲህ እንዲሉ አዟቸዋል፡-
} ﻭَﺃُﻭﺣِﻲَ ﺇِﻟَﻲَّ ﻫَﺬَﺍ ﺍﻟْﻘُﺮْﺁﻥُ ﻟِﺄُﻧْﺬِﺭَﻛُﻢْ ﺑِﻪِ ﻭَﻣَﻦْ ﺑَﻠَﻎَ { ( ﺍﻷﻧﻌﺎﻡ : 19 )
‹‹ይህም ቁርኣን እናንተንና የደረሰውን ሰው ሁሉ በርሱ ላስጠነቅቅበት ወደኔ ተወረደ (በላቸው)››
(አል አንዓም 19)
ስለጋኔኖችም ሲናገር እንዲህ ይላል
} ﺇِﻧَّﺎ ﺳَﻤِﻌْﻨَﺎ ﻗُﺮْﺁﻧًﺎ ﻋَﺠَﺒًﺎ }{ ﻳَﻬْﺪِﻱ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﺮُّﺷْﺪِ ﻓَﺂﻣَﻨَّﺎ ﺑِﻪِ { ( ﺍﻟﺠﻦ : 1 ، 2 )
‹እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም፤ ወደ ቀጥታ መንገድ የሚመራን (ቁርአን ሰማን)፡፡ በእርሱም አመንን፡፡ ›› (አል ጂን 1-2)
አላህ እንዲህ ብሏል፦
} ﻭَﻣَﻦْ ﻳَﺒْﺘَﻎِ ﻏَﻴْﺮَ ﺍﻟْﺈِﺳْﻠَﺎﻡِ ﺩِﻳﻨًﺎ ﻓَﻠَﻦْ ﻳُﻘْﺒَﻞَ ﻣِﻨْﻪُ { ( ﺁﻝ ﻋﻤﺮﺍﻥ : 85 )
‹‹ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም›› (አል ዒምራን 85)
} ﺇِﻧَّﺎ ﺃَﻧْﺰَﻟْﻨَﺎ ﺇِﻟَﻴْﻚَ ﺍﻟْﻜِﺘَﺎﺏَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻟِﺘَﺤْﻜُﻢَ ﺑَﻴْﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﺑِﻤَﺎ ﺃَﺭَﺍﻙَ ﺍﻟﻠَّﻪُ { ( ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ : 105 )
‹‹እኛ በሰዎች መካከል አላህ ባሳወቀህ ልትፈርድ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት አወረድን፡፡›› አል ኒሳእ 1ዐ5
ቀደም ብሎ በተጠቀሰውም የአህሉል ኪታቦችን መፅሐፍ ማንበብ በሚከለክለው የጃቢር ሀዲሰ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
( . . . « ﻭﺍﻟﺬﻱ ﻧﻔﺴﻲ ﺑﻴﺪﻩ ﻟﻮ ﺃﻥ ﻣﻮﺳﻰ ﻛﺎﻥ ﺣﻴًّﺎ ﻣﺎ ﻭﺳﻌﻪ ﺇﻻ ﺃﻥ ﻳﺘﺒﻌﻨﻲ » ﻭﺍﻩ ﺍﻹﻣﺎﻡ ﺃﺣﻤﺪ ﻓﻲ ﺍﻟﻤﺴﻨﺪ : 3 / 387 ، ﻭﻏﻴﺮﻩ )
“ነፍሴ በእጁ ባለው ጌታ እምላለሁ ሙሳ እንኳን ህያው ቢሆን እኔን ከመከተል ውጭ አማራጭ የለውም፡፡” (ሙስነድ አህመድ 3/387 )
•┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈•
https://t.me/tenbihat
© ተንቢሀት

