Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ፊታዋ ለሙስሊም ሴቶች ከሴት ብልት የሚወጣ እርጥበት (ፈሳሽን )የተመለከተ ሼይኽ ዐብዱል ዐዚዝ ኢብን ባዝ


ፊታዋ ለሙስሊም ሴቶች
===============
1.3 ከሴት ብልት የሚወጣ እርጥበት (ፈሳሽን )የተመለከተ ሑክም

ጥያቄ
______
ከአንድ ሙስሊም ምሁር( ዓሊም)የሰማሁት ከሴት ብልት የሚወጣ ፈሳሽ ንጹህ እንደሆነ ነበር ።ይህንን ፈትዋ በመንተራስም ከብልቴ እርጥበት ባየሁ ቁጥር ሶላት ለመስገድ ልብሴን አልቀይርም ነበር።በዚህ ዓይነት ብዙ ጊዜ ካሳለፍኩኝ በኋላ ከሌላ ምሁር( ዓሊም)ከሴት ብልት የሚወጣ ፊሳሽ( እርጥበት )ነጃሳ እንደሆነ ሰማሁ ታዲያ የትኛው አባባል ነው ትክክለኛው?

መልስ
______
ከሁለቱ ቀዳዳዎች በየትኛውም በኩል የሚወጣ ፈሳሽም ይሁን ሌላ ነገር ውድእ የሚያስፈታ ሲሆን ይህ ነገር የነካው የሰውነት ክፍልም ሆነ ልብስ የሚነጀስ በመሆኑ መታጠብ ይኖርበታል። ሆኖም ግን ይህ ፈሳሽን ሆነ ሌላ ነገር በተከታታይና ያልማቋረጥ የሚወጣ ከሆነ የኢስቲሐዳን( የበሽታ ደምን )እና ያለማቋረጥ የሚፈስን ሽንት ሕግ በመንተራስ ነው ተፈፃሚ የሆነው ።ይህም ማለት ያለማቋረጥ ከሴት ብልት የሚወጣ ደም ወይም ሽንት ካለ ሴትዬዋ በየሶላት ወቅቱ የብልቱን አካባቢና ልብሷን በማጠብ ና እቦታው ላይ ጨርቅ ወይም ጥጥ በማድረግ አዲስ ወዱእ ካደረገች በኋላ መስገድ ይኖርባታል ።ይህ ብይን የመነጨው የነቢዩት ﷺ ንግግር በመንተራስ ሲሆን ኢስቲሐዳን አስመልክተው እንዲሚከተለው ብለዋል ፦••••በእያንዳንዱ ሶላት ወዱእ ማድረግ ያስፊልጋል። "ከዚህ ክስተት ለየት የሚል ሁኔታ ካለ በተከታታይ ከፊንጢጣ የሚወጣ አየር ፈስ ነው።በዚህ ጊዜ ውዱእ ማድረግ ብቻ በቂ ሲሆን ልብስንና የሰውነትን ክፍል ማጠብ አስፈላጊ አይደለም ፦
{{ሼይኽ ዐብዱል ዐዚዝ ኢብን ባዝ }}

Post a Comment

0 Comments