Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ጉንዳኗ ተሻለች?

ጉንዳኗ ተሻለች?
አቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ እንደተናገረው የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላምና ውዳሴ በርሳቸው ላይ ይሁንና) እንዲህ አሉ: –
« ሱለይማን (ዐለይሂ ሰላም) (ከሕዝቦቹ) ጋር ሆኖ አላህ ዝናብ እንዲሰጣቸው ሊለምኑት ወጡ ። ከዚያም አንዲት ጉንዳን በጀርባዋ ሆና እግሮቿን ወደላይ ዘርግታ እንዲህ ብላ ዱዐ ስታደርግ (ሱለይማን) ሰሟት " አላህ ሆይ ! እኛ ከፍጥረታቶችክ መካከል (አነድ) ፍጥሮች ነን ። ያለ ውሃ መኖር አንችልም (ስጠን) " ከዚያም ነቢዩ ሱለይማን (ዐለይሂ ሰላም) ለሕዘቦቹ እንዲህ አላቸው :– " ተመለሱ በሌሎች (በጉንዳኗ) ዱዐ ዝናብን ተሰጥቷቿል " ... »
(በሌላ ዘገባ "ወዲያው ዝናብ ዘነበ" )
[አሕመድ ዘግበውታል አል ሃኪም "ሶሒሕ" ብለውታል ] ከቡሉጘል መራም "ሰላቱል አሰቲስቃ" የተወሰደ
ቁምነገሩ,,,
ይቺ ከፍጥረታት ሁሉ እጅጉን አነስተኛ ነጥብ የሆነችው ጉንዳን አላህ ሆይ ዝናብ ስጠን ብላ ወሊዮች ጋር አልሄደችም የነቢዩ ዳውድ (ዐለይሂ ሰላም) ቀብርም ጋር ሄዳ መለመን አላስፈለጋትም ። ምክንያቱም አላህን አንድን ነገር ለመጠየቅ አዋሳኝ ፣ አማካይ ፣ አማላጅ እንደማያስፈልግ ታውቃለችና ነው።
የዛሬዎቹ "ሙስሊም ነን" ባዮች ታዲያ ምነው ከዚች ጉንዳን እንኳን መሻል ተሳናቸው ?

Alter Native

Post a Comment

0 Comments