Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

ነብዩን(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ማሞገስን በንግድነት መጠቀም እንዴት ይታያል


ለሸህ ኡሰይሚን (አላህ ይዘንላቸውናጥያቄ ቀረበላቸው ጥያቄ፡ነብዩን(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምማሞገስን በንግድነት መጠቀምእንዴት ይታያልመልስ፡ይህ ሐራም ነው፡፡ የነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምሙገሳ በሁለት እንደሚከፈል መታወቅ አለበት፡-አንደኛው፡ሳያጋንኑና ከልክ ሳያልፉ በሚገባቸው ነገር ማሞገስ ነው፡፡ ይህ ችግር የለውም፡፡ ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምከስነምግባራቸው በሚገባቸው ነገር ቢሞገሱ ችግር የለውም፡፡ሁለተኛው፡ከልክ ያለፈ ሙገሳ ነው፡፡ ይህን ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምእንዲህ በማለት ከልክለዋል፡፡ “ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ እንዳላቁት አታልቁኝ እኔ ባሪያ ነኝ የአላህ ባሪያና መልእክተኛው በሉኝ” ብለዋል፡፡ ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምእርዳታ የጠየቃቸውን የሚረዱ (የሚደርሱለትናቸው፡፡ የተቸገረን ሰው ዱዓ ይቀበላሉ የአዱንያና የአኺራ ተቆጣጣሪ ናቸው፡፡ ገይብን ያውቃሉ እና የመሳሰሉትን በማለት ነቢዩን ማሞገስ ሐራም ነው፡፡ ከኢስላም ወደ ሚያስወጣው ሽርኩል አክበር ደረጃም ሊደርስ ይችላል፡፡ ነቢዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምከልክ አሳልፎ ማሞገስ አይቻልም፡፡ ነቢዩ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምከልክለውታልና፡፡ ወደ ጥያቄው ጭብጥ እንመለስና የሚፈቀደውንም ሙገሳ ቢሆን በንግድነት መጠቀም ሐራም ነው፡፡ ምክንያቱም ነቢዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምከስነ ምግባራቸው ምስጉን ከሆነ ባህሪያቸውና ቅኑን መንገድ ከመምራታቸው በሚገባቸው ነገር እሳቸውንማሞገስ ኢባዳ ነው፡፡ ዒባዳ ደግሞ ወደ አላህ የሚቃረቡበት መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ለዓለማዊ ጥቅም መፈለጊያ መዋል የለበትም፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡፡ مَن كَانَ يُرِيدُ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا وَزِينَتَهَا نُوَفِّ إِلَيْهِمْ أَعْمَٰلَهُمْ فِيهَا وَهُمْ فِيهَا لَا يُبْخَسُونَ أُو۟لَٰٓئِكَ ٱلَّذِينَ لَيْسَ لَهُمْ فِى ٱلْءَاخِرَةِ إِلَّا ٱلنَّارُ ۖ وَحَبِطَ مَا صَنَعُوا۟ فِيهَا وَبَٰطِلٌ مَّا كَانُوا۟ يَعْمَلُونَቅርቢቱን ሕይወትና ጌጧን የሚሹ የሆኑን ሰዎች ስራዎቻቸውን (ምንዳዋንበርሷ ውስጥ ወደነሱ እንሞላላቸዋለን፡፡ እነሱም በርሷ ውስጥ ምንም አይጎድልባቸውም በመጨረሻይቱ ዓለም ከእሳት በቀር የሌላቸው ናቸው የሰሩትም ስራ በርሷ ውስጥ ተበላሸ (በቅርቢቱ ዓለምይሰሩት የነበሩትም በጎ ስራ ብልሹ ነው፡፡” (ሁድ 1115-16) ትክክለኛውን መንገድ የሚመራ አላህ ብቻ ነው፡፡