Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts


ነት" ማውራት የፈለገ ዳዒ ጉዳዩን ሳያብራራ ቢያልፈው " አጎደለ" ወይም " አላስረዳም" መባሉ ሊገርም አይገባም! ! እንደውም ተገቢ ነው!!
የዳዒ አላማም ማደናገርና ታዳሚውን ወዥንብር ውስጥ መንከር ወይም በነበረበት ውዥንብር ላይ ማቆየት ሳይሆን ማስረዳትና ጭብጥን ማስጨበጥ ነውና " አስረጂ" መሆኑ "የጥራት ደረጃውን" ከፍ ያረገዋል! !
አድማጭና አንባቢውም ማብራሪያው በጠፋ ግዜ ማብራሪያ እና ቅጥያ መፈለጉ እጅግ ጤናማ አካሄድ ነው— ሊያሰወቅስ ይቅርና! !
በርግጥ በዚህ ጉዳይ "ብቻ" ሰዎችን በኢኽዋንነት መፈረጅ ተገቢ አይደለም።
ቀደምት ኢማሞቻችን አላህ ከዐርሽ በላይ መሆኑን ሲገልፁ "በዛቱ " የሚለውን ቅጥያ ጨምረዋል—ብልሹ የሆኑ የጀህሚያ አቋሞችን ለማስወገድና ጉዳዩን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ። እንጂ ቁርአንና ሓዲስ ላይ "በዛቱ" የሚል ቅጥያ አይገኝም!!
በተጨማሪም ቁርአንን غير مخلوق
(ፍጡር ( የተፈጠረ)አይደለም)
ብለው ቁርአንና ሓዲስ ላይ በማይገኝ ጭማሪና ቅጥያ ገልፀዋል — مخلوق
(ፍጡር ነው) የሚሉ ጠማሞች በወቀቱ በመገኘታቸው ......
غير مخلوق
የሚለው ንግግር ራሱ ቢድዓ መሆኑን ግልፅ ያረጉ ኢማሞች ከመኖራቸው ጋር! !
እናም ፣ ቁርአንና ሓዲስ ላይ የመጡ ነገሮችን መጀመሪያ በመጡበት መልኩ መረዳት በደበዘዘበት ወቅት ቅጥያዎችን ( ሸሪዐው በሚፈቅደው መልኩ) ጨማምሮ ማብራራቱ እጅግ አስፈላጊ ነው። ይህንን ቅጥያ መጠበቅና መጠየቅ ደግሞ ጤናማ አመለካከት ሊነፈገው የሚገባ አይደለም! !

Muhammedsirage MuhammedNur Gidey

Post a Comment

0 Comments