Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

የሸዋልን ፆም ለጀመሩ እህቶች አስፈላጊ ጥቆማዎች




☞ የሸዋልን ፆም ለጀመሩ እህቶች አስፈላጊ ጥቆማዎች
الحمد لله والصلاة والسلام على رسول الله وعلى آله وصحبه، أما بعـد:
ከሸዋል ፆም ጋር በተያያዘ ብዙ እህቶች ከሚጠይቋቸው ጥያቄዎች በመነሳት አምስት ጥቆማዎች ይኖሩኛል፤
1) ቀዳ ያለባት ሴት ከቀዳና ከሸዋል ሱና የትኛውን ታስቀድም?
☞ በሀይድ ወይም በወሊድ ደም ምክኒያት ረመዳንን አሟልታ ያልፆመች ሴት፤ ከሸዋል ስድስት ቀናት መፆምን አስመለክቶ በሀዲስ የተጠቀሰውን የአንድ አመት ፆም ምንዳ ለማግኘት አጅሩን እንደሚያገኝ ቃል የተገባለት ረመዳንን ካሟላ በኋላ የፆመው ሰው ስለሆነ፤ ቅድሚያ ረመዳንን መፆም ግድ ስለሚል በተቻላት መጠን ከሸዋል ሱና በፊት የረመዳንን ቀዷ ለማጠናቀቅ መሞከር ይኖርባታል።
📚 የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ይህንን በማስመልከት እንዲህ ብሏል፤ ¹ «ከረመዳን የተወሰኑ ቀናት ያሉበት ሰው በቅድሚያ እነሱን ሊፆምና ከዛ በኃላ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን ሊፆም ይገባል፤ ምክኒያቱም ረመዳንን አስከትሎ ከሸዋል ስድስት ቀን ሊፆም የሚችለው ረመዳንን አሟልቶ ከፆመ ነው።» ፈታወለጅናህ 10/392
ይህንን መተግበር ሴቶች ያለባችውን ቀዷ በጊዜ መክፈል ይችሉ ዘንድ ያበረታቸዋል።
2) የረመዳንን ወር በሙሉ ካልፆመችስ?
📚 ሸይኽ ኡሰይሚን እንደገለፁት²
በወሊድ ወይም በተለያዩ በሽታዎች ምክኒያት ረመዳንን ሙሉዉን መፆም ያልቻለች ሴት ሸዋልን ቀዳ በማውጣት ከጨረሰችና ስድስቱን የሱና ቀናት መፆም የምትችልበት ጊዜ ሸዋል ውስጥ ካላገኘች የዘገየችው ከአቅም በላይ በሆነ ምክኒያት (ደሩራ) ስለሆነ ቀጣዩ የዙልቂእዳ ወር ከገባ በኃላም ቢሆን በሸዋል ሱና ነይታ ፆሟን ብታሟላው ኢን ሻ አላህ አጅሩን ታገኛለች። ይህንን መልእክት ያዘለውን የሸይኽ ኡሰይሚን ፈትዋ በመጅሙኡል ፈታዋ 20/19 ያገኙታል
3) ቀዳና የሸዋል ሱናን በአንድ ኒያ መፆም፦
📚 ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁላህ (ኑሩን አለደርብ)² የጥያቄና መልስ ፕሮግራም ላይ ተጠይቀው ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፤ «የስድስቱን ቀናት ፆም ከፈለገች በቅድሚያ ቀዳ አውጥታ በመቀጠል ሱናውን ፆም ትፁም። በሸዋል ወር ቀዳ አውጥታ ስድስቱን ቀናትም ከፆመች ትልቅ ኸይር ነው። የስድስቱን የሸዋል ቀናት ፆም ከቀዳ ጋር በአንድ ኒያ ብትፆም ግን የስድስቱን ቀናት አጅር ታገኛለች ብዬ አላስብም። የሸዋል ፆም የሚፆመው በተገደበ ጊዜ ሲሆን እራሱን የቻለ ኒያ ይፈልጋል።»
ስለዚህም ሁለቱን በአንድ ላይ መፆም ሳይሆን ቅድሚያ ረመዳንን አሟልቶ ሱናውን ፆም መጀመር ተገቢ ነው።
4) የሸዋል ወር ሳያልቅ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ቀናት ቢያልፉስ?
☞ ብዙ ሴቶች የሸዋል ፆም የሚባለው ወሩ እንደገባ ያሉት ስድስት ቀናት ብቻ ይመስሏቸዋል። ይህ ስህተት ነው። በሀዲሱ የተጠቀሰው ምንዳ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናት የፆመን ሰው ሁሉ ይመለከታል። ይህ ደግሞ መጀመሪያም መጨረሻም በመካከልም ሊሆን ይችላል።
5) የሸዋልን ፆም አከታትሎ መፆም፦
☞ ሸዋል እንደገባ ብዙ ሰዎች አከታትለው በመፆም ይጨርሳሉ። ይህም ስንፍናን ለማስወገድና በረመዳን ያካበቱትን የመፆም ብቃት ላለማጣት ከማሰብ ነው። ነገር ግን በተቃራኒው ሰኞና ሀሙስ እንዲሁም አያመልቢድ በመፆም ሱና ፆም የመፆምን ልምድ ማዳበርም መልካም ነው። አንዳንድ ሴቶች አከታትለው መፆማቸው ግዴታ ስለሚመስላቸው ከመፆም ይሳነፋሉ። ይህ ሊታረም የሚገባው ግንዛቤ ነው።
አላህ ፆማችንን ይቀበለን ዘንድ እማፀነዋለሁ!
አቡጁነይድ ሸዋል 4/10/1436
————// ————
¹ (...والذي ينبغي لمن كان علي شيء من أيام رمضان أن يصومها أولا ثم يصوم ستة أيام من شوال ؛ لأنه لا يتحقق له اتباع صيام رمضان لست من شوال إلا إذا كان قد أكمل صيامه . وبالله التوفيق وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم ) فتاوى الجنة الدائمة 10/392
² سئل الشيخ ابن عثيمين رحمه الله تعالى عما إذا كان على المرأة دين من رمضان فهل يجوز أن تقدم الست على الدين أم الدين على الست ؟
فأجاب بقوله : "إذا كان على المرأة قضاء من رمضان فإنها لا تصوم الستة أيام من شوال إلا بعد القضاء ، ذلك لأن النبي صلى الله عليه وسلم يقول : ( من صام رمضان ثم أتبعه ستا من شوال ) ومن عليها قضاء من رمضان لم تكن صامت رمضان فلا يحصل لها ثواب الأيام الست إلا بعد أن تنتهي من القضاء ، فلو فرض أن القضاء استوعب جميع شوال ، مثل أن تكون امرأة نفساء ولم تصم يوما من رمضان ، ثم شرعت في قضاء الصوم في شوال ولم تنته إلا بعد دخول شهر ذي القعدة فإنها تصوم الأيام الستة ، ويكون لها أجر من صامها في شوال ، لأن تأخيرها هنا للضرورة وهو ( أي صيامها للست في شوال) متعذر، فصار لها الأجر" انتهى مجموع الفتاوى 20/19
³ سئل الشيخ ابن باز رحمه الله
هل يجوز للمرأة الجمع بين صيام ستة أيام من شوال وقضاء ما عليها من رمضان في هذه الأيام الستة بنية القضاء والأجر معاً، أم لا بد من القضاء أولاً ثم صيام ستة أيام من شوال؟
نعم، تبدأ بالقضاء، ثم تصوم الست إذا أرادت، الست نافلة، فإذا قضت في شوال ما عليها ثم صامت الست من شوال فهذا خير عظيم، وأما أن تصوم الست بنية القضاء والست فلا يظهر لنا أنه يحصل لها بذلك أجر الست، الست تحتاج إلى نية خاصة في أيام مخصوصة.
http://www.binbaz.org.sa/node/13470
والله تعالى المسؤول أن يوفقنا لما يحب ويرضى .

Abujunaid Salah Ahmed