Header Ads Widget

Ticker

6/recent/ticker-posts

የአብሬት ሸህ እና ደርግ



የአብሬት ሸህ እና ደርግ
አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው የሁሉ ፈጣሪ፣ ህያው፣የማይሞተው፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ ነው፡፡ ሰሞኑን ጉዞ ወደ አብሬት ብለው ሰዎች የሚሄዱለት የአብሬት ሸይኽ በመባል ይታወቃሉ፡፡ አገራችን ላይ በጣም ድንበር ከሚታለፍባቸው ግለሰቦች ውስጥ ከቶፕ 5 ውስጥ ናቸው፡፡ 
እዚህ ትምህርት ላይ ማንሳት የፈለግኩት ምን አይነት ሰው ነበሩ? የሚለውን አይደለም፡፡ ነገር ግን መጥቀስ የምፈልገው ምን ያህል ድንበር እንደታለፈባቸው ነው፡፡
የአብሬት ሸይኽ አዲስ አበባ አውቶብስ ተራ ወረድ ብሎ ያለ አካባቢጠቅላይ ቢሮየሚባል ቦታ ውስጥ እራሳቸውን አሟቸው በተኙበት ከሳቸውሙሪዶችአንዱ ቤቱን 7 ጊዜ ዞሮ ፊዳ ልሁን እኔ ብሎ እራሱን በቢላዋ አርዶ ገድሏል፡፡
ሌላው የአብሬት ሸይኽን በጣም ብዙ ሰዎች ለአላህ ብቻ የሚገባውን አምልኮ ሲፈፅሙላቸው ይታያል፡፡ አሳዛኙ ግን የአብሬት ሸይኽም ይሁን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለራሳቸውም ይሁን ለጠየቃቸው ጥቅምን ማምጣት፣ መስጠት አይችሉም፡፡ ከጉዳትም እራሳቸውንም ሆነ ጠብቀኝ ያላቸውን መከላከል አይችሉም፡፡
የአብሬት ሸይኽ ደርግ ወስዷቸው እርምጃ እንደወሰደባቸው ቤተሰቦቻቸውም የእሳቸውን ሞት ሁሉ ተቀብለው ተቀምጠው ሳለ፣ ተከታዬቻቸውአባባ ይመጣሉአባባ አልሞቱምእያሉ ብዙ ችግር ውስጥ ገብተዋል፡፡
አምልኮ ከደርግ እራሳቸውን ማስጣል ለማይችሉት ለደካማው አብሬት አይገባም፡፡ ይሄ ሺርክ ነው፡፡
አምልኮ ሃያል፣ ህያው፣ የማይሞት፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ እና ብቻ ነው የሚገባው፡፡

Post a Comment

0 Comments